የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ለመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም ውጤታማነት ሁሉን አቀፍ ጥረት ማድረግ ይገባል - ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ

Mar 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ)፦ በመንገድ ዘርፍ የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ሁሉን አቀፍ ጥረት ማድረግ እንደሚገባ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ።

የመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄዷል።

የኢትዮጵያ የመንገድ ሽፋን የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራሙ በ1989 ዓ.ም ከነበረበት 23 ሺህ ኪሎ ሜትር አሁን ላይ ወደ 171 ሺህ ማድረስ መቻሉ ተገልጿል።

የግንባታ ግብዓት ዋጋ መናር፣ የወሰን ማስከበር፣ የመንገድ ጥገና ላይ ያሉ ክፍተቶች (የማሽነሪ እና የባለሙያ እጥረት) እና የፕሮጀክት አመራር እና የሀገር በቀል የሥራ ተቋራጮች ያሉ ውስንነቶች የዘርፉ ማነቆዎች መሆናቸው በውይይቱ ላይ ተነስቷል።

የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በመንገድ ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችን በአፋጣኝ መፍታት ልዩ ትኩረት እንደሚያሻው አመልክተዋል።

የወሰን ማስከበር ሥራዎችን በታቀደ መልኩ መፈጸም፣ የመንገድ ጥገናን በተቀመጠለት ጊዜ ማጠናቀቅ ማጠናቀቅ፣ የሰው ኃይል አቅም ግንባታ እና የግሉ ዘርፍ በመንገድ ግንባታ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እንደሚገባ አመልክተዋል።

ሚኒስቴሩ ለመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም መሻሻል አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራህማን (ኢ/ር)፤ በመንገድ ዘርፍ ያሉ ውጤቶች ለማስቀጠል እና ተግዳሮቶቹን በዘላቂነት ለመፍታት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የዘርፉን ውጤታማነት ሁሉን አቀፍ ጥረት እና የባለድርሻ አካላት የጋራ ጥረት ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።

የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ከውይይቱ በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ምርምር ማዕከልን መጎብኘታቸውን ከአስተዳደሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026