የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ለመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም ውጤታማነት ሁሉን አቀፍ ጥረት ማድረግ ይገባል - ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ

Mar 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ)፦ በመንገድ ዘርፍ የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ሁሉን አቀፍ ጥረት ማድረግ እንደሚገባ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገለጹ።

የመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄዷል።

የኢትዮጵያ የመንገድ ሽፋን የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራሙ በ1989 ዓ.ም ከነበረበት 23 ሺህ ኪሎ ሜትር አሁን ላይ ወደ 171 ሺህ ማድረስ መቻሉ ተገልጿል።

የግንባታ ግብዓት ዋጋ መናር፣ የወሰን ማስከበር፣ የመንገድ ጥገና ላይ ያሉ ክፍተቶች (የማሽነሪ እና የባለሙያ እጥረት) እና የፕሮጀክት አመራር እና የሀገር በቀል የሥራ ተቋራጮች ያሉ ውስንነቶች የዘርፉ ማነቆዎች መሆናቸው በውይይቱ ላይ ተነስቷል።

የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በመንገድ ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችን በአፋጣኝ መፍታት ልዩ ትኩረት እንደሚያሻው አመልክተዋል።

የወሰን ማስከበር ሥራዎችን በታቀደ መልኩ መፈጸም፣ የመንገድ ጥገናን በተቀመጠለት ጊዜ ማጠናቀቅ ማጠናቀቅ፣ የሰው ኃይል አቅም ግንባታ እና የግሉ ዘርፍ በመንገድ ግንባታ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እንደሚገባ አመልክተዋል።

ሚኒስቴሩ ለመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም መሻሻል አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራህማን (ኢ/ር)፤ በመንገድ ዘርፍ ያሉ ውጤቶች ለማስቀጠል እና ተግዳሮቶቹን በዘላቂነት ለመፍታት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የዘርፉን ውጤታማነት ሁሉን አቀፍ ጥረት እና የባለድርሻ አካላት የጋራ ጥረት ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።

የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ከውይይቱ በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ምርምር ማዕከልን መጎብኘታቸውን ከአስተዳደሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.