የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢትዮጵያ በአፍሪካ አንደኛ ስንዴ አምራች ሀገር ሆናለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Mar 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በአፍሪካ አንደኛ ስንዴ አምራች ሀገር መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በኢኮኖሚው ዘርፍ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።

በማብራሪያቸውም መንግሥት የ10 ዓመት የልማት ዕቅድ ማዘጋጀቱን ገልጸው፤ ይህን እቅድ ከግብ ለማድረስ በትጋት እየሰራ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት 8 ነጥብ 4 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ አቅዳ እየሰራች መሆኗን ጠቅሰው፤ ባለፉት ስምንት ወራት በእያንዳንዱ ዘርፍ የተመዘገቡ አመላካች ውጤቶች ከታቀደው በላይ ማሳካት እንደሚቻል የሚያሳዩ ናቸው ሲሉ ገልጸዋል።

በግብርናው ዘርፍ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች የሰብል ሽፋን አምና ከነበረበት 17 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር ወደ 20 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር ማደጉን ገልጸዋል።

በኩታ ገጠም እርሻ አምና የታረሰው 8 ነጥብ 7 ሚሊዮን እንደነበር ጠቅሰው፤ ዘንድሮ 11 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሄክታር መታረሱን ተናግረዋል።

በስንዴ ልማት በመኸር 4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር፣ በበጋ መስኖ 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር መልማቱን ጠቅሰዋል።

በዚህም 7 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በስንዴ ሰብል የሸፈነች ሲሆን ከዚህም ከ300 ሚሊዮን ኩንታል ያላነሰ ምርት ይጠበቃል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ ስንዴ አምራች ሀገር መሆኗንም አክለዋል።

ስንዴ ከውጭ ማስግባት የለባትም የሚል አቋም ለነበራቸው ሁሉ ከፍተኛ እመርታ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ የማይካድ ሀቅ ነው ብለዋል።

በቡና፣ በአትክልትና ፍራፍሬ በቅባት እህሎች ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ እመርታ መመዝገቡን ተናግረዋል።

በቡናው ዘርፍም ለውጭ ከቀረበ ምርት ባለፈው ዓመት 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ጠቅሰው፤ ባለፉት ስምንት ወራት ብቻ 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን ገልጸዋል።

በሚቀጥሉት አራት ወራትም አሁን ባለን አካሄድ ከፈጸምን 2 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ገቢ ማስመዝገብ እንችላለን ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.