የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢትዮጵያ በተመድ የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ የነቃ ተሳትፎ ታደርጋለች - ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር)

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አዲሱ የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ የነቃ ተሳትፎ እንደምታደርግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትሩ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ መልዕክተኛ አማንዲፕ ሲንግ ጊል(ዶ /ር) ጋር ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ መልዕክተኛ አማንዲፕ ሲንግ ጊል(ዶ /ር) ተመድ በዲጂታላይዜሽን እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ ባቋቋመው አዲስ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ አንድ አካል ሆና በንቃት እንድትሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።


ሚኒስትሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታላይዜሽን አስፈላጊነት ለሀገር እድገት ሊጫወት የሚችለውን ቁልፍ ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት በቴክኖሎጂ ዙሪያ የሚሰሩ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና መሰል ተቋማት አስቀድሞ እንዲቋቋሙ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የተመድ አዲሱ ኢኒሼቲቭ አካል መሆኗ ቁልፍ ተግባር እንደሆነ በመግለጽ በንቃት እንደምትሳተፍ አመልክተዋል።

አዲሱ የተመድ የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ ወጥ የሆነ አስተዳደር ለማውጣትና የአቅም ግንባት ሥራዎችን ለመሥራት መቋቋሙን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026