
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አዲሱ የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ የነቃ ተሳትፎ እንደምታደርግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ መልዕክተኛ አማንዲፕ ሲንግ ጊል(ዶ /ር) ጋር ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ መልዕክተኛ አማንዲፕ ሲንግ ጊል(ዶ /ር) ተመድ በዲጂታላይዜሽን እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ ባቋቋመው አዲስ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ አንድ አካል ሆና በንቃት እንድትሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

ሚኒስትሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታላይዜሽን አስፈላጊነት ለሀገር እድገት ሊጫወት የሚችለውን ቁልፍ ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት በቴክኖሎጂ ዙሪያ የሚሰሩ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና መሰል ተቋማት አስቀድሞ እንዲቋቋሙ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የተመድ አዲሱ ኢኒሼቲቭ አካል መሆኗ ቁልፍ ተግባር እንደሆነ በመግለጽ በንቃት እንደምትሳተፍ አመልክተዋል።
አዲሱ የተመድ የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ ወጥ የሆነ አስተዳደር ለማውጣትና የአቅም ግንባት ሥራዎችን ለመሥራት መቋቋሙን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...
Jul 22, 2026
ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...
Jul 21, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...
Jul 15, 2026