የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢኒስቲትዩቱ የተመድ የዲጂታል ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ቢሮ አባል መሆን የሚያስችል ጠንካራ አቅም አለው - አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር)

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2017 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በቅርቡ በተቋቋመው የተባበሩት መንግስታት የዲጂታል ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ቢሮ (UN-ODET) አባል ለመሆን የሚያስችል ጠንካራ ተቋማዊ ቁመና ላይ እንደሚገኝ የተመድ ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የቢሮው ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) ገለጹ።

በአማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) የተመራ ልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝቷል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ለልዑኩ አቀባበል አድርገዋል።

ሁለቱ ወገኖች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት እና ትግበራ በትብብር መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይም ተወያይተዋል።

ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ለልዑኩ ኢንስቲትዩቱ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን መሰረት በማድረግ እየተገበራቸው ያሉ ኢኒሼቲቮችን አስመልክቶ ገልጸዋል።

ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የመፍትሄ አማራጮች እና ኢኒሼቲቮች መጠቀም የሚያስችለውን የጋራ ትብብር ለመፍጠር ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና በድርጅቱ በተቋቋመው አዲስ የዲጂታል ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ቢሮ (UN-ODET) ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) ኢንስቲትዩቱ በአጭር ጊዜ በኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት ላይ የመጣውን ከፍተኛ ለውጥ አድንቀዋል።

ተቋሙ በድርጅቱ በተቋቋመው አዲስ የዲጂታል ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ቢሮ (UN-ODET) አባል የመሆን ጠንካራ አቅም እንዳለው መግለጻቸውን የኢኒስቲትዩቱ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.