
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2017 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በቅርቡ በተቋቋመው የተባበሩት መንግስታት የዲጂታል ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ቢሮ (UN-ODET) አባል ለመሆን የሚያስችል ጠንካራ ተቋማዊ ቁመና ላይ እንደሚገኝ የተመድ ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የቢሮው ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) ገለጹ።
በአማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) የተመራ ልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝቷል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ለልዑኩ አቀባበል አድርገዋል።
ሁለቱ ወገኖች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት እና ትግበራ በትብብር መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይም ተወያይተዋል።
ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ለልዑኩ ኢንስቲትዩቱ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን መሰረት በማድረግ እየተገበራቸው ያሉ ኢኒሼቲቮችን አስመልክቶ ገልጸዋል።
ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የመፍትሄ አማራጮች እና ኢኒሼቲቮች መጠቀም የሚያስችለውን የጋራ ትብብር ለመፍጠር ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና በድርጅቱ በተቋቋመው አዲስ የዲጂታል ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ቢሮ (UN-ODET) ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) ኢንስቲትዩቱ በአጭር ጊዜ በኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት ላይ የመጣውን ከፍተኛ ለውጥ አድንቀዋል።
ተቋሙ በድርጅቱ በተቋቋመው አዲስ የዲጂታል ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ቢሮ (UN-ODET) አባል የመሆን ጠንካራ አቅም እንዳለው መግለጻቸውን የኢኒስቲትዩቱ መረጃ ያመለክታል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026