
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2017 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በቅርቡ በተቋቋመው የተባበሩት መንግስታት የዲጂታል ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ቢሮ (UN-ODET) አባል ለመሆን የሚያስችል ጠንካራ ተቋማዊ ቁመና ላይ እንደሚገኝ የተመድ ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የቢሮው ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) ገለጹ።
በአማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) የተመራ ልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝቷል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ለልዑኩ አቀባበል አድርገዋል።
ሁለቱ ወገኖች በሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት እና ትግበራ በትብብር መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይም ተወያይተዋል።
ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ለልዑኩ ኢንስቲትዩቱ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን መሰረት በማድረግ እየተገበራቸው ያሉ ኢኒሼቲቮችን አስመልክቶ ገልጸዋል።
ኢንስቲትዩቱ የተለያዩ ሰው ሰራሽ አስተውሎት የመፍትሄ አማራጮች እና ኢኒሼቲቮች መጠቀም የሚያስችለውን የጋራ ትብብር ለመፍጠር ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና በድርጅቱ በተቋቋመው አዲስ የዲጂታል ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ቢሮ (UN-ODET) ልዩ ልዑክ አማንዲፕ ሲንግ ጊል (ዶ/ር) ኢንስቲትዩቱ በአጭር ጊዜ በኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት ላይ የመጣውን ከፍተኛ ለውጥ አድንቀዋል።
ተቋሙ በድርጅቱ በተቋቋመው አዲስ የዲጂታል ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ቢሮ (UN-ODET) አባል የመሆን ጠንካራ አቅም እንዳለው መግለጻቸውን የኢኒስቲትዩቱ መረጃ ያመለክታል።
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፦ በጉራጌ ዞን የመኸር አዝመራን ውጤታማ ለማድረግ ለሰብል እንክብካቤ፣ ለኩታገጠም እርሻና ለግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትኩ...
Jul 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ የተፈጥሮ ሀብትና የዱር እንስሳት ጥበቃ ሥራዎች ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ያላቸውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎሉ ተግባራት...
Jul 22, 2026
ድሬደዋ፣ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦በድሬደዋ አስተዳደር በበጀት አመቱ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የአስተ...
Jul 21, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፦ መንግሥት የኢትዮጵያን የሎጂስቲክስ ዘርፍ በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማ...
Jul 15, 2026