የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ ሳተላይቶች ያመነጯቸው መረጃዎች ለኢኮኖሚ ዕድገት የላቀ ፋይዳ እያበረከቱ ነው - ኢንስቲትዩቱ

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ያመጠቀቻቸው ሁለት ሳተላይቶች ያመነጯቸው መረጃዎች ለኢኮኖሚ ዕድገት የላቀ ፋይዳ እያበረከቱ እንደሚገኝ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

ኢትዮጵያ ETRSS-1’ እና ኢቲ ስማርት አር ኤስ ኤስ (ET-Smart-RSS) የተሰኙ ሁለት የመሬት ምልከታ ሳተላይቶችን ማምጠቋ የሚታወስ ነው።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ እነዚህ ሳተላይቶች ወደ ህዋ ከመጠቁ በኋላ በርካታ ጥቅም እያስገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ሳተላይቶቹ ለግብርና፣ ለደንና አየር ንብረት ጥበቃ፣ ለማዕድን፣ ለተፈጥሮ ሀብት ጥናትና መረጃ ለመሰብሰብ እንዲሁም ለመሰረተ ልማት ዝርጋታ የሚሆኑ ጥራት ያላቸው መረጃዎችን መላካቸውን ተናግረዋል።

ኢንሰቲትዩቱ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ሀይል እንዲኖር ለማስቻል ከዩንቨርሲቲዎች ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

እንዲሁም የልጆች የስፔስ ክህሎት ማእከል በማቋቋም በክረምት ወራት ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊዎች እያሰለጠነ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂም የቅንጦት ሳይሆን ኢትዮጵያ ተወዳዳሪና ውጤታማ እድገት ለመፍጠር አጋዥ ዘርፍ መሆኑን አብራርተዋል።

የነዚህን ሳተላይቶች መረጃ በመጠቀም ለኢኮኖሚያዊ እድገቱ መረጋገጥ የላቀ ፋይዳ ያላቸው ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አመላክተዋል።

ኢንስቲትዩቱ 3ተኛዋን ሳተላይት ለማምጠቅ የመጀመሪያ ምእራፍ መጠናቀቁን ገልጸው ይህም ከፍተኛ የምስል ጥራት ያለው ሳተላይት መሆኑን ተናግረዋል።


በኢንስቲትዩቱ የካርታ ስራ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ቴዎድሮስ ካሳሁን በበኩላቸው በነዚህ ሳተላይቶች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የችግኝ ማፍያ እና መትከያ ቦታዎችን በሚመለከት የጂኦስፓሻል መረጃዎችን መሰብሰብ መቻሉን ገልጸዋል።

ሳተላይቶቹ የውሃ አካላትን መረጃዎች ለመተንተን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳስገኙ የገለጹት ደግሞ በኢንስቲትዩቱ የዲጂታል ኢሜጅ ፕሮሰሲንግ መሪ ስራ አስፈጻሚ ተስፋዬ ዳኜ ናቸው።


በተመረጡ ሃይቆች ላይ መረጃዎችን በመሰብሰብ እና በመተንተን ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተደራሽ እየሆኑ መሆኑንም አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026