የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ አውደ ርዕይና ባዛር በአርባ ምንጭ ከተማ ተከፈተ

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ አውደ ርዕይና ባዛር በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ተከፍቷል።

በአውደ ርዕዩና ባዛሩ ላይ ከ60 በላይ መካከለኛ፣ አነስተኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ምርቶቻቸውን አቅርበዋል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳዬ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቦጋለ ቦሼ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት አውደ ርዕይና ባዛሩን ከፍተዋል።


ዓላማው የኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሀገር ኢኮኖሚ ያለውን ሚና ለማላቅና ተኪ ምርቶች በጥራትና በስፋት እንዲመረቱ በማድረግ የውጭ ምንዛሬን ለማዳንና ለማስገኘት እንደሆነም ተመላክቷል።

በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የመጡ ለውጦችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግም ከመርሃ ግብሩ መረዳት ተችሏል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የጋሞ ዞን እና የአርባ ምንጭ ከተማ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026