
አርባ ምንጭ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ አውደ ርዕይና ባዛር በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ተከፍቷል።
በአውደ ርዕዩና ባዛሩ ላይ ከ60 በላይ መካከለኛ፣ አነስተኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ምርቶቻቸውን አቅርበዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳዬ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቦጋለ ቦሼ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት አውደ ርዕይና ባዛሩን ከፍተዋል።

ዓላማው የኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሀገር ኢኮኖሚ ያለውን ሚና ለማላቅና ተኪ ምርቶች በጥራትና በስፋት እንዲመረቱ በማድረግ የውጭ ምንዛሬን ለማዳንና ለማስገኘት እንደሆነም ተመላክቷል።
በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የመጡ ለውጦችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግም ከመርሃ ግብሩ መረዳት ተችሏል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የጋሞ ዞን እና የአርባ ምንጭ ከተማ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026