የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ እስካሁን ከስድስት መቶ በላይ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ ተመልሰዋል - ኢንስቲትዩቱ

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 27/2017 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ እስካሁን ከስድስት መቶ በላይ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መመለሳቸውን የአምራች ኢንዱስተሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሚልኬሳ ጃጋማ(ዶ/ር)ገለጹ።


የመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች በአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተሞች በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተጨባጭ ውጤት ያስመዘገቡ ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል።

የጉብኝቱ አላማ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ወደ ስራ የተመለሱ ኢንዱስትሪዎችን የስራ እንቅስቃሴ ለመመልከት ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስተሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሚልኬሳ ጃጋማ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም በጉልህ አሳድጓል።

ንቅናቄው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት፣ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በጥራትና በብዛት በማምረት ከፍተኛ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ጠቁመዋል።

በንቅናቄው በተፈጠሩ ቅንጅታዊ አሰራሮች የዘርፉን ማነቆዎች በመለየት ተዘግተው የነበሩ ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርት መመለሳቸውን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ እስካሁን ስድስት መቶ ሃያ አምስት የሚጠጉ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መመለሳቸውንም አክለዋል።

ከንቅናቄው በፊት የነበረው የማምረት አቅም 48 በመቶ እንደነበር ገልጸው በንቅናቄው አማካኝነት አሁን ላይ የማመረት አቅም 61 ነጥብ 08 በመቶ መድረሱን አመላክተዋል።

እንዲሁም ከዚህ ቀደም የአምራች ዘርፉ የሚመራበት ፖሊሲ እንዳልነበር አስታውሰው፤ በዚሁ ንቅናቄ ዘርፉ የሚመራበት አዲስ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

ከፖሊሲው በመነሳትም የዘርፉን ችግሮች የሚፈቱ በርካታ ስትራቴጂዎች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።


የዘደይ አግሮ ኢንዱስተሪ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ የዚችአለም ካሳ ንቅናቄው በህብረተሰቡ ውስጥ የሀገር ውስጥ ምርት ተጠቀሚነት እንዲያድግ ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተናግረዋል።

እንዲሁም ከዚህ ቀደም ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በሀገር ውስጥ እየተመረቱ ነው የሚለውን ግንዛቤ መፍጠር የቻልንበት ነው ሲሉም አስታውቀዋል።


የ ቢ ኤም ኤፍ የባህልና ዘመናዊ አልባሳት ማምረቻ ስራ አስኪያጅ ማርስአለም ሁሴን በበኩላቸው፤ ንቅናቄው ከተኛንበት ያነቃን ነው ብለዋል።

የማምረት አቅማቸው እንዲያድግ እንዲሁም በስራ እድል ፈጠራ ላይ የነበራቸው አስተዋጽኦ ከፍ እንዲልም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።


በንቅንቄው የተፈጠረው ቅንጅታዊ አሰራር ማነቆዎችን እየፈታልን ነው ያሉት ደግሞ የአዳኣል ኢንዱስትሪያል ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አዳነ በርሄ ናቸው።

የኬርኤዢ የቆዳ ውጤቶች ማምረቻ ስራ አስኪያጅ ዘላለም መርአዊ በየአመቱ የሚካሄደው ኤክስፖ ከፍተኛ መነቃቃት መፍጠሩን ገልጿል።

እንዲሁም የእርስ በእርስ ትውውቅና እና የገበያ ትስስር እንዲጎለብት ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከተን ተናግሯል።


የእጅግ ጥበብ ስራ አስኪጅ እጅጋየሁ ሀይለጊዮርጊስም ንቅናቄው በተለያዩ ኤግዚቢሽኖች ምርታቸውን ለማስተዋወቅ እድል እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።

እንዲሁም በንቅናቄው አማካኝነት እየተደረገ ያለው ድጋፍ መልካም መሆኑንም ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026