የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

አርሶ አደሮቹ መሬታቸውን በመስኖና በመኸር እርሻ በማልማት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገለጹ

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አክሱም፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ መሬታቸውን በበጋ መስኖና በመኸር እርሻ ማልማት መቻላቸው በግብርና ምርታቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን በትግራይ ክልል ማዕከላዊ ዞን የላዕላይ ማይጨው ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።


አርሶ አደሮቹ በመጪው የመኸር ወቅት የተሻለ ምርት ለመሰብሰብ የሚያስችላቸውን ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።


በወረዳው የ"ድራ" ገጠር ቀበሌ ነዋሪ ሴት አርሶ አደር አበባ ገብረክርስቶስ እንዳሉት፣ በበጋ ለመስኖ ልማት ሲጠቀሙበት የነበረውን ማሳ ምርቱን በማንሳት ለመኸሩ አዝመራ የምንጣሮ ስራ በማከናወን ደጋግመው በማረስ አዘጋጅተዋል።


በምርት ዘመኑ የተሻለ ምርት ለመሰብሰብ ሁለት ኩንታል ዘመናዊ ማዳበሪያ ከገበሬዎች የህብረት ስራ ማህበር ገዝተው ያዘጋጁ ሲሆን፣በተጓዳኝም ከተፈጥሮ ፍግ፣ ከተለያዩ ተረፈ ምርቶችና ከቅጠላ ቅጠል ብስባሽ ኮምፖስት ማዘጋጀታቸውን ገልፀዋል።


በላዕላይ ማይጨው ወረዳ የ"መዶገ" ገጠር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ኪዳነ አበራ በበኩላቸው በ2017/18 የምርት ዘመን የተሻለ ምርት ለመሰብሰብ ማሳቸውን ደጋግመው ከማለስለስ ባለፈ ሁለት ኩንታል የተፈጥሮ ኮምፖስትን ጨምሮ 6 ኩንታል ዘመናዊ ማዳበሪያ ማዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።


በመጀመሪያ ዙር በመስኖ ለምቶ የነበረውን የበቆሎ ምርት በመሰብሰብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው ለመኸሩም የእርሻ ማሳቸውን ደጋግመው ማረሳቸውንና የዝናብ ውሃን እንዲያሰርግ በሚረዳ መልኩ ማሰናዳታቸውን ገልጸዋል።


በበጋ ወቅት የእርሻ መሬትን ደጋግሞ ማረስና ማለስለስ አረምን ከምንጩ ለማድረቅ እንደሚረዳ የገለጹት ደግሞ በወረዳው የመስኖና አዝርዕት ባለሙያ አቶ ብርሃነ ገብረመስቀል ናቸው።


የወረዳው አርሶ አደሮች ማሳቸውን መልሰው መላልሰው የማረስና የማለስለስ ስራ በወቅቱ መጀመራቸው የሚበረታታ ነው ያሉት ባለሙያው ወደ ሥራ ያልገቡ ካሉም ቶሎ እንዲገቡ አሳስበዋል።


በወረዳው የገጠር ልማት ጽህፈት ቤት በቁጠባ ዘርፍ የህብረት ስራና ገበያ አስተባባሪ አቶ ሹሻይ አሰፋ በበኩላቸው፣ ለ2017/18 የምርት ዘመን አርሶ አደሩ በአቅራቢያው ዘመናዊ ማዳበሪያ እንዲያገኝ በ15 የገጠር ቀበሌዎች የመጋዘንና የመሸጫ ማእከላት ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ ናቸው ብለዋል።


ለወረዳው 21 ሺህ 500 ኩንታል ሰው ሰራሽ ማዳበሪያ በህብረት ስራ ዩኒየን በኩል መቅረቡንም ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026