የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ጥራት ያለው የፋይናንስና ኦዲት ሪፖርቶችን በማያቀርቡ የኦዲትና ሂሳብ ባለሙያዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል- ቦርዱ

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ጥራት ያለው የፋይናንስና ኦዲት ሪፖርቶችን በማያቀርቡ የኦዲትና ሂሳብ ባለሙያዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ የኢትዮጵያ ሒሳብ አያያዝ እና ኦዲት ቦርድ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ሒሳብ አያያዝ እና ኦዲት ቦርድ ከተሰጡት ስልጣንና ተግባራት መካከል የሂሳብ ሙያ ማህበራት፣ በሒሳብና ኦዲት ሙያ ላይ በመሰማራት ለህዝብ የሂሳብ ሙያ አገልግሎት መስጠት የሚፈልጉ ባለሙያዎችን እና ድርጅቶችን መስፈርት በማውጣት ፍቃድ መስጠት መከታተልና መደገፍ ይገኙበታል።

በተጨማሪም ከተቋማት የሚመጡ የፋይናንስና ኦዲት ሪፖርቶች ደረጃቸውን ጠብቀው መከናወናቸውን የማረጋገጥና የመቆጣጠር ሥራዎችን ማከናወንም እንዲሁ።

የኢትዮጵያ ሒሳብ አያያዝ እና ኦዲት ቦርድ ተጠባባቂ ዋና ዳይሬክተር ፍቃዱ አጎናፍር ለኢዜአ እንዳሉት ቦርዱ የተለያዩ አለም አቀፍ ደረጃዎችን የመቀበልና የማስተዋወቅ ስራዎች እየሰራ ይገኛል።

ባለፉት ስምንት ወራት በአለም አቀፍ ደረጃ የወጡ ከዘላቂነትና አየር ንብረት ጋር የተያያዙ አዳዲስ ደረጃዎችን ለባንኮች፣ ለኢንሹራንሶች፣ የመንግስት የልማት ድርጅቶችና ለዘርፉ ሙያ ማህበራት ማስተዋወቅ መቻሉን ተናግረዋል።

የፋይናንስና የኦዲት ጥራት ግምገማ በማድረግ የተለያየ አይነት የፋይናንስና ኦዲት ሪፖርት ዝግጅትን ለማስቀረት እየሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።

ቦርዱ የባለሙያዎች ፍቃድ እድሳት እንደሚያደርግ ገልፀው፤ በተያዘው በጀት አመት እስካሁን ባለው ከ600 በላይ ባለሙያዎች ፍቃዳቸውን ማደሳቸውን ተናግረዋል።

እስካሁን ባለው በኦንላይን ሂደቱን አጠናቀው የእድሳት ምስክር ወረቀታቸውን ከቦርዱ ሲወስዱ መቆየታቸውን አንስተው ከቀጣይ አመት ጀምሮ የምስክር ወረቀቱንም ባሉበት ሆነው ማግኘት የሚችሉበት አሰራር እየተዘረጋ መሆኑን ጠቁመዋል።

ቦርዱ በኢትዮጵያ ጥራት ያለው የፋይናንስና ኦዲት ሪፖርት እንዲዘጋጅ ለማድረግ ሙያዊ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የባለሙያዎች ፍቃድ አሰጣጥ በቦርዱ በኩል መሰጠት ያለበት ቢሆንም እስካሁን ባለው በክልሎች ፍቃድ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው ፤ ወጥነት ባለው መስፈርትና አሰራር ፍቃድ ለመስጠት የሚያስችል ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ወጥነት ያለው አሰራር መተግበር የታክስ ስወራና ሌሎች ማጭበርበሮችን ለማስቀረት የሚያስችልና የኦዲትና ፋይናንስ ጥራትን ለማስጠበቅ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸው፤ ጥራት ያለው ሪፖርቶችን በማያቀርቡ የኦዲትና ሂሳብ ባለሙያዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።

ለቦርዱ የሚቀርበውን ሪፖርት ከወረቀት አሰራር ወደ ቴክኖሎጂ ለመቀየር ሶፍትዌር ማበልፀግ የሚያስችል ስራ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ለቦርዱ የሪፖርት ጥራት ግምገማ በማድረግ የተለያዩ ማስተካከያ እንዲያደርጉ ለተቋማት ግብረ መልስ እንደሚሰጥ አንስተው በቀጣይ ግን ከማስተማር ባለፈ የተጠያቂነት አሰራርን የማስፈን ስራ ይሰራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026