የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በምዕራብ ኦሞ ዞን ይርኒ ቀበሌ የተገነባ የጸሐይ ኃይል ማመንጫ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

Apr 8, 2025

IDOPRESS

ጀሙ፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምዕራብ ኦሞ ዞን ይርኒ ቀበሌ ከ5ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የጸሐይ ኃይል ማመንጫ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

ፕሮጀክቱ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቅንጅት በ60 ሚሊዮን ብር የተገነባ ነው።


የተመረቀው ፕሮጀክት 100 ኪሎ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚችል መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ(ዶ/ር) ተናግረዋል።

ኢኮኖሚያዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መሰል ፕሮጀክቶች ትልቅ ትርጉም ስላላቸው ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲሁም የክልሉና የዞን የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.