
ጀሙ፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምዕራብ ኦሞ ዞን ይርኒ ቀበሌ ከ5ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የጸሐይ ኃይል ማመንጫ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ፕሮጀክቱ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቅንጅት በ60 ሚሊዮን ብር የተገነባ ነው።

የተመረቀው ፕሮጀክት 100 ኪሎ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚችል መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ(ዶ/ር) ተናግረዋል።
ኢኮኖሚያዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መሰል ፕሮጀክቶች ትልቅ ትርጉም ስላላቸው ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲሁም የክልሉና የዞን የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026