የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

Apr 8, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፤ መጋቢት 29/2017 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።

የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ማጠናከር ላይ ያለመ የምክክር መድረክ ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል፡፡


ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት ክልሉ የሀገር ውስጥና የውጪ ባለሀብቶችን በዘርፉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችሉ አማራጮችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በማስፋትና በመደገፍ ለስኬት እንዲበቁ ማስቻል ለስራ እድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተናግረዋል፡፡

በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ያሉ ተግዳሮቶችን መፍታት፣ የማምረቻና የመሸጫ ቦታዎች ማዘጋጀትን ጨምሮ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በክልሉ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራም ገልፀዋል፡፡

በወተት፣ በንብ ማነብና በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የሚያመርቱትን ምርት እሴት በመጨመር ምርታቸውን ለገበያ እንዲያቀርቡ ማድረግ እንደሚገባም ጠቁመዋል።


የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር አለባቸው ንጉሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው በኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችንና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን የሚያመላክት እንዲሁም የድጋፍ ማዕቀፍን መሰረት ያደረገ ጥናት በመከናወን ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት እንደሚሰራም ነው ያስረዱት፡፡


የክልሉ ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ እንደገለፁት በክልሉ ተወዳዳሪና አምራች ኢንተርፕራይዞችን በማፍራት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።

በዚህም ለ1 ሺህ 286 አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ሁሉን አቀፍ ድጋፍ በመስጠት ወደ ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የክልል፣ የዞንና፣ የልዩ ወረዳ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በተለያየ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.