የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

Apr 8, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፤ መጋቢት 29/2017 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።

የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ማጠናከር ላይ ያለመ የምክክር መድረክ ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ተካሄዷል፡፡


ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት ክልሉ የሀገር ውስጥና የውጪ ባለሀብቶችን በዘርፉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችሉ አማራጮችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በማስፋትና በመደገፍ ለስኬት እንዲበቁ ማስቻል ለስራ እድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተናግረዋል፡፡

በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ያሉ ተግዳሮቶችን መፍታት፣ የማምረቻና የመሸጫ ቦታዎች ማዘጋጀትን ጨምሮ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሚስተዋሉ ማነቆዎችን ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በክልሉ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራም ገልፀዋል፡፡

በወተት፣ በንብ ማነብና በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የሚያመርቱትን ምርት እሴት በመጨመር ምርታቸውን ለገበያ እንዲያቀርቡ ማድረግ እንደሚገባም ጠቁመዋል።


የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር አለባቸው ንጉሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው በኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችንና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን የሚያመላክት እንዲሁም የድጋፍ ማዕቀፍን መሰረት ያደረገ ጥናት በመከናወን ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት እንደሚሰራም ነው ያስረዱት፡፡


የክልሉ ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ እንደገለፁት በክልሉ ተወዳዳሪና አምራች ኢንተርፕራይዞችን በማፍራት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።

በዚህም ለ1 ሺህ 286 አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ሁሉን አቀፍ ድጋፍ በመስጠት ወደ ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የክልል፣ የዞንና፣ የልዩ ወረዳ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በተለያየ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026