የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርቶችን ከማስተዋወቅ ባለፈ ለገበያ ትስስርም ትልቅ አስተዋጽኦ አለው

Apr 9, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ የገበያ ትስስር በመፍጠርና ተኪ ምርቶችን በማምረት ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች ገለጹ።

በአርባ ምንጭ ከተማ በተካሄደው ክልል-አቀፍ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ የተሳተፉ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንደገለጹት፣ ንቅናቄው ከተጀመረ ወዲህ የዘርፉ ችግር በመሠረታዊነት እየተፈታ ነው።

አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል የዊን ውሃ ፋብሪካ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወገኔ ዳና የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርቶችን በጥራትና በስፋት በማምረት ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል።

በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ በሚገኘው የውሃ ማምረቻ ፋብሪካ ከ100 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ጠቅሰው፣ ንቅናቄው የገበያ ትስስር ከመፍጠር ባለፈ ለውሃ መያዣ የሚያስፈልገውን እቃ በራስ አቅም ለማምረት እንዳነሳሳቸው ተናግረዋል።


በአሁኑ ወቅትም የማሽን ተከላ ሥራ ላይ መሆናቸውን ነው ያስታወቁት

በእጅ ጥበብ የሚሠሩ ሸሚዝ፣ ፎጣ፣ ቀሚስ፣ ቲሸርት፣ ኮፍያና መሰል አልባሳትን በማምረት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ገበያ እያቀረቡ መሆኑን የተናገረው ደግሞ በአርባ ምንጭ ከተማ የሚገኘው ቤሬ የሐር ልማት ድርጅት የምርት ክፍል ሃላፊ ወጣት ዳዊት ደሌ ነው።


የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርቶቻቸውን በማስተዋወቅ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የገበያ ትስስር እንደፈጠረላቸው ተናግሯል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ቦጋለ ቦሼ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በክልሉ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እየተነቃቃ መጥቷል።

ንቅናቄውን ተከትሎ በተኪና ወጪ ምርቶች ላይ የባለሀብቶችን ተሳትፎ ከማሳደግ ባለፈ በገበያ ላይ ተወዳዳሪና ጥራት ያለው ምርት እንዲያመርቱ እያገዘ መሆኑንም ጠቅሰዋል።


አምራች ኢንዱስትሪው ከግብአት አቅርቦት፣ ከገበያ ትስስርና ምርታማነትን ከማሻሻልና ከማሳደግ አንጻር ያለበት ችግር እንዲፈታም ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ዶክተር ቦጋለ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት በሚል መሪ ሃሳብ በአርባ ምንጭ ከተማ ለሦስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ ኤግዚቢሽን እና ባዛር ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026