የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርቶችን ከማስተዋወቅ ባለፈ ለገበያ ትስስርም ትልቅ አስተዋጽኦ አለው

Apr 9, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ የገበያ ትስስር በመፍጠርና ተኪ ምርቶችን በማምረት ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች ገለጹ።

በአርባ ምንጭ ከተማ በተካሄደው ክልል-አቀፍ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ የተሳተፉ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንደገለጹት፣ ንቅናቄው ከተጀመረ ወዲህ የዘርፉ ችግር በመሠረታዊነት እየተፈታ ነው።

አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል የዊን ውሃ ፋብሪካ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወገኔ ዳና የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርቶችን በጥራትና በስፋት በማምረት ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል።

በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ በሚገኘው የውሃ ማምረቻ ፋብሪካ ከ100 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ጠቅሰው፣ ንቅናቄው የገበያ ትስስር ከመፍጠር ባለፈ ለውሃ መያዣ የሚያስፈልገውን እቃ በራስ አቅም ለማምረት እንዳነሳሳቸው ተናግረዋል።


በአሁኑ ወቅትም የማሽን ተከላ ሥራ ላይ መሆናቸውን ነው ያስታወቁት

በእጅ ጥበብ የሚሠሩ ሸሚዝ፣ ፎጣ፣ ቀሚስ፣ ቲሸርት፣ ኮፍያና መሰል አልባሳትን በማምረት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ገበያ እያቀረቡ መሆኑን የተናገረው ደግሞ በአርባ ምንጭ ከተማ የሚገኘው ቤሬ የሐር ልማት ድርጅት የምርት ክፍል ሃላፊ ወጣት ዳዊት ደሌ ነው።


የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርቶቻቸውን በማስተዋወቅ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የገበያ ትስስር እንደፈጠረላቸው ተናግሯል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ቦጋለ ቦሼ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በክልሉ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እየተነቃቃ መጥቷል።

ንቅናቄውን ተከትሎ በተኪና ወጪ ምርቶች ላይ የባለሀብቶችን ተሳትፎ ከማሳደግ ባለፈ በገበያ ላይ ተወዳዳሪና ጥራት ያለው ምርት እንዲያመርቱ እያገዘ መሆኑንም ጠቅሰዋል።


አምራች ኢንዱስትሪው ከግብአት አቅርቦት፣ ከገበያ ትስስርና ምርታማነትን ከማሻሻልና ከማሳደግ አንጻር ያለበት ችግር እንዲፈታም ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ዶክተር ቦጋለ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት በሚል መሪ ሃሳብ በአርባ ምንጭ ከተማ ለሦስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ ኤግዚቢሽን እና ባዛር ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026