
ባህርዳር፤መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በመጪው የፋሲካ በዓል ወቅት በፍጆታ ምርት ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይከሰት ከወዲሁ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
ከዝግጅቱም መካከል ጊዜያዊ የገበያ ማዕከላት፣የንግድ ትርኢትና ባዛሮች እንደሚገኙበት ተመልክቷል።
የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢብራሂም ሙሃመድ(ዶ/ር) ማምሻውን በሰጡት መግለጫ፤ በቅርቡ በሚከበረው የፋሲካ በዓል የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ቀደም ሲል በሌማት ትሩፋት ላይ በተከናወነው ስራ እንቁላል፣ ዶሮና ሌሎች የግብርና ምርቶችን ከደላላ ነጻ በሆነ የግብይት አሰራር ለማቅረብ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም የደለቡ ሠንጋ በሬዎች፣ በግ፣ ፍየልና ሌሎች ለበዓሉ የሚውሉ ግብአቶች ከተለያዩ የገጠር አካባቢዎች እንዲገቡ ቀድሞ የማመቻቸት ስራ መከናወኑን አስረድተዋል።
እንደ ዘይት፣ስኳርና ዱቄት ያሉ የኢንዱስትሪ ምርቶች በበቂ ሁኔታ እየቀረቡ በመሆኑ ሸማቹ ህብረተሰብ ተረጋግቶ እንዲገበያይ አስታውቀዋል።
የተሳለጠ ግብይት እንዲኖርና ታልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይከሰት በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ጊዜያዊ የገበያ ማዕከላት መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፤ የንግድ ትርኢትና ባዛር ለማሰናዳት በሂደት ላይ እንዲሆኑ አረጋግጠዋል።
በየደረጃው የሚገኙ የቢሮው መዋቅር አመራር አባላትና ባለሙያዎች የተሳለጠ ግብይት እንዲኖር አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026