የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ በመጪው የበዓል ወቅት በፍጆታ ምርት ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይከሰት ዝግጅት እየተደረገ ነው

Apr 9, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በመጪው የፋሲካ በዓል ወቅት በፍጆታ ምርት ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይከሰት ከወዲሁ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።


ከዝግጅቱም መካከል ጊዜያዊ የገበያ ማዕከላት፣የንግድ ትርኢትና ባዛሮች እንደሚገኙበት ተመልክቷል።


የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢብራሂም ሙሃመድ(ዶ/ር) ማምሻውን በሰጡት መግለጫ፤ በቅርቡ በሚከበረው የፋሲካ በዓል የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።


በዚህም ቀደም ሲል በሌማት ትሩፋት ላይ በተከናወነው ስራ እንቁላል፣ ዶሮና ሌሎች የግብርና ምርቶችን ከደላላ ነጻ በሆነ የግብይት አሰራር ለማቅረብ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን ጠቅሰዋል።


በተጨማሪም የደለቡ ሠንጋ በሬዎች፣ በግ፣ ፍየልና ሌሎች ለበዓሉ የሚውሉ ግብአቶች ከተለያዩ የገጠር አካባቢዎች እንዲገቡ ቀድሞ የማመቻቸት ስራ መከናወኑን አስረድተዋል።


እንደ ዘይት፣ስኳርና ዱቄት ያሉ የኢንዱስትሪ ምርቶች በበቂ ሁኔታ እየቀረቡ በመሆኑ ሸማቹ ህብረተሰብ ተረጋግቶ እንዲገበያይ አስታውቀዋል።


የተሳለጠ ግብይት እንዲኖርና ታልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይከሰት በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ጊዜያዊ የገበያ ማዕከላት መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፤ የንግድ ትርኢትና ባዛር ለማሰናዳት በሂደት ላይ እንዲሆኑ አረጋግጠዋል።


በየደረጃው የሚገኙ የቢሮው መዋቅር አመራር አባላትና ባለሙያዎች የተሳለጠ ግብይት እንዲኖር አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026