አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎች እድገት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።
አቶ መላኩ አለበል ሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ የተባለ ተቋምን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።
ሚኒስትሩ በጉብኝቱ ወቅት መንግስት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ፋብሪካዎች እንዲስፋፉ እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡
ዛሬ የተጎበኘው ሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ ከውጭ የሚገባውን የውሀ ቆጣሪ በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል፡፡
መንግስት ይበለጠ ተኪ ምርትን የሚያመርቱ ፉብራካዎች እንዲስፋፉ እና ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፉና ክትትሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።
የሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ ስራ እስኪያጅ ዐይንእሸት አስረስ(ዶ/ር) መንግስት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ድርጅቱ ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል፡፡