
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎች እድገት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።
አቶ መላኩ አለበል ሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ የተባለ ተቋምን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።
ሚኒስትሩ በጉብኝቱ ወቅት መንግስት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ፋብሪካዎች እንዲስፋፉ እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡
ዛሬ የተጎበኘው ሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ ከውጭ የሚገባውን የውሀ ቆጣሪ በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል፡፡
መንግስት ይበለጠ ተኪ ምርትን የሚያመርቱ ፉብራካዎች እንዲስፋፉ እና ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፉና ክትትሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።
የሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ ስራ እስኪያጅ ዐይንእሸት አስረስ(ዶ/ር) መንግስት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ድርጅቱ ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026