
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎች እድገት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።
አቶ መላኩ አለበል ሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ የተባለ ተቋምን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።
ሚኒስትሩ በጉብኝቱ ወቅት መንግስት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለሚተኩ አምራች ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ፋብሪካዎች እንዲስፋፉ እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡
ዛሬ የተጎበኘው ሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ ከውጭ የሚገባውን የውሀ ቆጣሪ በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል፡፡
መንግስት ይበለጠ ተኪ ምርትን የሚያመርቱ ፉብራካዎች እንዲስፋፉ እና ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፉና ክትትሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።
የሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ ስራ እስኪያጅ ዐይንእሸት አስረስ(ዶ/ር) መንግስት በሚያደርግላቸው ድጋፍ ድርጅቱ ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026