የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ኢትዮ ቴሌኮም በባሌ ሮቤና አሰላ ከተሞች የአምስተኛውን ትውልድ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት አስጀመረ

Apr 11, 2025

IDOPRESS

ሮቤ፤ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም በሮቤና አሰላ ከተሞች የአምስተኛውን ትውልድ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት ዛሬ አስጀመረ።

ኩባኒያው ለህዝብ የሚሰጠውን አገልግሎት ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የደቡብ ምሥራቅ ሪጅን ጽህፈት ቤቱን በባሌ ሮቤ በአዲስ መልክ ሥራ ማስጀመሩ ተመልክቷል።

በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩና የኩባንያው ከፍተኛ አመራር አባላት እንዲሁም የሮቤ ከተማና የባሌ ዞን አመራሮችና የአገልግሎቱ ደንበኞች ተገኝተዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ፍሬህይወት ታምሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ኩባኒያው አገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻል ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን የማድረግ ጉዞ ላይ ይገኛል።

የአምስተኛው ትውልድ ኔትወርክ አገልግሎት የዓለማችን ፈጣንና ቀልጣፋ የኔትወርክ አገልግሎት መሆኑን አንስተው ዛሬ አገልግሎት የጀመሩትን ጨምሮ በኢትዮጵያ በ16 ከተሞች አገልግሎቱን ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

የአምስተኛው ትውልድ (5ጂ) የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት ደንበኞች ዘመኑን የሚመጥን ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

ዛሬ በሮቤና አሰላ ከተሞች የተጀመረው የአምስተኛው ትውልድ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት በከተሞቹና በአካባቢው የሚከናወኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስራዎችን በተሻለ ደረጃ ለማከናወን የሚያግዝ ነውም ብለዋል።

ኩባኒያው ለህዝብ የሚሰጠውን አገልግሎት ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግና ለማዘመን የደቡብ ደቡብ ምሥራቅ ሪጅን ጽህፈት ቤቱን በባሌ ሮቤ በአዲስ መልክ ሥራ ማስጀመሩንም አክለዋል።

የሪጅኑ መከፈት የተቀናጀ የቴሌኮምና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን መሰረተ ልማትን ለማህበረሰቡ ለማቅረብ እየተደረገ የሚገኘውን ጥረት በተሻለ ሁኔታ እንደሚያግዝም አመልክተዋል።

በኢትዮ ቴሌኮም የደቡብ ደቡብ ምሥራቅ ሪጅን ጽህፈት ቤት የሁለቱን የባሌ ዞኖችና ከፊል አርሲ ዞኖችን እንደሚያካቲት ከኩባኒያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።


#Ethiopian_News_Agency


#ኢዜአ


#Ethiopia

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026