
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 5/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው እየተመዘገበ ያለው ስኬት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት የመንግስት የልማት ድርጅቶች አፈጻጸም በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉንም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
የ2017 በጀት ዓመት የሦስተኛው ሩብ ዓመት የ100 ቀን አፈጻጸምና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራ ያለፉት ዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።ፀ
የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ የማክሮ ኢኮኖሚና የዘርፎች አፈጻጸም አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም የዘንድሮው አመት የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የተደረገበት በመሆኑ ከሌሎቹ አመታት ለየት ያለ መሆኑን ገልጸዋል።
በታሪክም ትልቁ የኢኮኖሚ ሪፎርም የተካሄደበት መሆኑን ጠቅሰው፤ የፊስካል ፖሊሲዎች ተግባራዊ መደረጋቸውንም ተናግረዋል።
እንዲሁም የእድገት አማራጮችን በማስፋት የግሉን ሴክተር ሚና ማሳደግ የሚያስችሉ የሪፎርም ስራዎች የተከናወኑበት መሆኑን ጠቁመዋል።
ከእድገት አፈጻጸም አንጻርም ያለፉት ዘጠኝ ወራት ጠንካራ ውጤት የተመዘገበበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
የዋጋ ንረትን በመቆጣጠር ረገድ ጥሩ ውጤት መመዝገቡን እና ካለፉት ወራት የቀነሰበት ሁኔታ መኖሩን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ የገቢ አቅምን ለማሳደግ የተሰራው ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸው፤ ከዚህ በላይ አጠናከሮ መቀጠል እንደሚገባ በመድረኩ መነሳቱን አስታውቀዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም ባለፉት ዘጠኝ ወራት የመንግስት የልማት ድርጅቶች አፈጻጸም በከፍተኛ ሁኔታ እድገት አስመዝግቧል ብለዋል።
በኤክስፖርት ረገድም መልካም አፈጻጸም መገኘቱን ጠቅሰው፤ አጠቃላይ የውጭ ምንዛሪ ክምችትና የባንኮች የምንዛሪ ግኝት መሻሻሉን ገልጸዋል።
የታክስ አስተዳደርን በማሻሻል እንዲሁም የታክስ ህግ ተገዥነትን በማሳደግ ረገድ የተከናወነው ስራ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡን አስታውቀዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻያው ሪፎርሙን ተከትሎ የሚመጣውን ጫና ለማስቀረት ከፍተኛ የበጀት ድጎማ መደረጉን ተናግረዋል።
ለአብነትም ለማዳበሪያ፣ ለነዳጅ፣ ለምግብ ዘይት፣ መድሀኒት እንዲሁም የመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ ጭማሪ መደረጉን አንስተዋል።
የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በሴክተሮች አፈጻጸም እና በኢኮኖሚ እድገት በመልካም የአፈጻጸም ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026