
መቀሌ፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ የግብርናውን ዘርፍ ማዘመንና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል ዘመናዊ አሰራርን መከተል ይገባል ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ገለጹ።
የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የግብርና ስትራቴጂክ ትግበራ እቅድን በተመለከተ በመቀሌ ከተማ ውይይት ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ፤ የግብርናውን ዘርፍ ማዘመንና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል ስትሬቴጅክ አሰራርን መከተል ይገባል ብለዋል።

የግብርና ልማትን ውጤታማ ለማድረግ በነበረው ስትራቴጂ እና ፖሊሲ መቀጠል የማይቻል በመሆኑ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማከል ውጤታማ ለመሆን መስራት ይገባል ብለዋል።
በመሆኑም በክልሉ የተፈጥሮ ሃብትን በመጠበቅ ዘመናዊ አሰራሮችን በመከተልና የተቀናጁ ጥረቶችን በማድረግ ማልማት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
በዚሁ ዙሪያ የተዘጋጀውን የስትራቴጂክ አተገባበር ውጤታማ ለማድረግና በተለይም የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር ለማሻሻል በቅንጅት መስራት ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ረገድ የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።

በጊዜያዊ አስተዳደሩ የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ሀላፊ እያሱ አብረሃ(ዶ/ር) የስትራቴጂው ትኩረት ግብርናን ማዘመንና ምርታማነትን ማሳደግ መሆኑን ገልጸዋል።
የግብርና ዘርፉን ማዘመንና ምርታማነትን ማሳደግ ከተቻለ ከተረጅነት በመውጣት በተለይም የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር ማሻሻል የሚያስችል ይሆናልም ነው ያሉት።
አጠቃላይ ስትራቴጅክ እቅዱ የመሬትና ውሃ አስተዳደር፣ እንስሳት እና የተፈጥሮ ሃብት ልማትን፣ የእርሻ ግብአት አጠቃቀምና ማዘመን እንዲሁም የገጠር ፋይናንስ አቅርቦትን ማእከል ያደረገ ስለመሆኑም አስረድተዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026