የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የግብርናውን ዘርፍ ማዘመንና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል ዘመናዊ አሰራርን መከተል ይገባል

Apr 15, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ የግብርናውን ዘርፍ ማዘመንና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል ዘመናዊ አሰራርን መከተል ይገባል ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ገለጹ።

የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የግብርና ስትራቴጂክ ትግበራ እቅድን በተመለከተ በመቀሌ ከተማ ውይይት ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ፤ የግብርናውን ዘርፍ ማዘመንና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል ስትሬቴጅክ አሰራርን መከተል ይገባል ብለዋል።


የግብርና ልማትን ውጤታማ ለማድረግ በነበረው ስትራቴጂ እና ፖሊሲ መቀጠል የማይቻል በመሆኑ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማከል ውጤታማ ለመሆን መስራት ይገባል ብለዋል።

በመሆኑም በክልሉ የተፈጥሮ ሃብትን በመጠበቅ ዘመናዊ አሰራሮችን በመከተልና የተቀናጁ ጥረቶችን በማድረግ ማልማት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።

በዚሁ ዙሪያ የተዘጋጀውን የስትራቴጂክ አተገባበር ውጤታማ ለማድረግና በተለይም የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር ለማሻሻል በቅንጅት መስራት ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ረገድ የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።


በጊዜያዊ አስተዳደሩ የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ሀላፊ እያሱ አብረሃ(ዶ/ር) የስትራቴጂው ትኩረት ግብርናን ማዘመንና ምርታማነትን ማሳደግ መሆኑን ገልጸዋል።

የግብርና ዘርፉን ማዘመንና ምርታማነትን ማሳደግ ከተቻለ ከተረጅነት በመውጣት በተለይም የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር ማሻሻል የሚያስችል ይሆናልም ነው ያሉት።

አጠቃላይ ስትራቴጅክ እቅዱ የመሬትና ውሃ አስተዳደር፣ እንስሳት እና የተፈጥሮ ሃብት ልማትን፣ የእርሻ ግብአት አጠቃቀምና ማዘመን እንዲሁም የገጠር ፋይናንስ አቅርቦትን ማእከል ያደረገ ስለመሆኑም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026