የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የግብርና ስትራቴጂክ እቅድ የአካባቢን ጸጋ ማዕከል ያደረገ ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ ያስችላል

Apr 15, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ሚያዝያ 6/2017(ኢዜአ)፡-በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተደደር የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ የተዘጋጀው የግብርና ስትራቴጂክ እቅድ ውሃና የአካባቢን ጸጋ ማዕከል ያደረገ ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ተገለጸ።

በአዲሱ የግብርና እና ገጠር ልማት ፖሊሲ ላይ በመመስረት ቢሮው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የግብርና ስትራቴጂክ እቅድ ላይ ዛሬ በመቀሌ ከተማ ውይይት ተካሄዷል።

በውይይት መድረኩ የክልሉ ጊዜያዊ አስተደደር የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ሀላፊ እያሱ አብረሃ(ዶ/ር ) እንዳሉት፥ የተዘጋጀው የግብርናና የተፈጥሮ ሀብት ስትራቴጂክ እቅድ የክልሉን የግብርና ምርት በዓይነትና ጥራት ተወዳዳሪነትን የሚያሳድግ ነው።

አዲሱ የግብርና እና ገጠር ልማት ፖሊሲ የሪፎርም ስራዎችን የሚያጠናክር፤ምርጥ ተሞክሮዎችን የሚያስፋፋ፣ውሃና የአካባቢን ጸጋ ማዕከል ያደረገ ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል።

ፖሊሲውን ማዕከል በማድረግ በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የተሰናዳው የግብርና ስትራቴጂክ ትግበራ እቅድ የክልሉን የመሬት አቀማመጥ፣የውሃና ተፈጥሮ ሃብት ጸጋዎች ላይ በመመስረት መሆኑን ተናግረዋል።

በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚያስችል መሆኑም ጠቅሰዋል።

እቅዱ በሚቀጥሉት 20 ዓመታት በግብርናው ዘርፍ መሰረታዊ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑን የገለጹት እያሱ አብረሀ (ዶ/ር )፥የመስኖና የእንስሳት ሃብት ልማት በእጥፍ የሚያሳድግ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በዚህም የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር ዘይቤን በዘላቂነት የሚያሻሽል መሆኑንም አክለዋል።

በቀጣይ የመኸር ወቅት ተግባራዊ መደረግ እንደሚጀመር ጠቁመው፤ በተለይ በዘርፉ ባለሃብቶችን በማሳተፍና ድጋፍ በማድረግ ሴቶችና ወጣቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ትኩረት መደረጉን አንስተዋል።

የግብርና ስትራቴጂክ ተግበራ እቅድ ካዘጋጁት የባልድርሻ አካል አባላት መካከል የዓይንሸት ተስፋይ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥እቅዱ በተፈጥሮና እንስሳት ሃብት ዙሪያ ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥር እና በግብርና ዘርፍ የወጣቶች ተጠቃሚነትን ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

እቅዱ የውስጥ ኢኮኖሚ አቅምን በማሳደግ የውሃ እና መሬት ብክነትን በመቀነስ በተለይ ትኩረት ያልተሰጠውን የክልሉ ተዳፋት ቦታዎች ለማልማትና የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጥን ትልቅ አቅጣጫ የያዘ መሆኑን የገለፁት ደግሞ ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ ገብረመድህን ወልደዋህድ (ዶ/ር ) ናቸው፡፡

እርሻ መሰረተ ልማትን በማስፋፋት የግል ባለሃብቱን ተሳትፎ የሚያበረታታ እና እርዳታ በማስቀረት ዘላቂ ልማት የሚያመጣ ስትራቴጂክ እቅድ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026