የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ 98 ሺህ ቶን የሚጠጋ የድንጋይ ከሰል ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቧል

Apr 15, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፣ ሚያዚያ 6/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በበጀት ዓመቱ ያለፉት ዘጠኝ ወራት 98 ሺህ ቶን የሚጠጋ የድንጋይ ከሰል ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ገብረማርያም ሰጠኝ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ከውጭ ከምታስገባቸው ምርቶች መካከል የድንጋይ ከሰል አንዱ ሲሆን በክልሉም በሰፊው ይገኛል።

ቀደም ሲል ሀብቱ ተገቢውን ትኩረት ተነፍጎት በመቆየቱ ለአካባቢውና ለሀገር ኢኮኖሚ የሚጠበቅበትን አስተዋጾ ሳያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል።

ይሁንና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ከዘርፉ የሚፈለገውን ጥቅም ለማግኘት በተወሰዱ እርምጃዎችና ወደምርት ሥራ በመገባቱ የድንጋይ ከሰሉን ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት 200 ሺህ ቶን የድንጋይ ከሰል ለማዕከላዊ ከበያ ለማቅረብ ታቅዶ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 98 ሺህ ቶን የሚጠጋ የድንጋይ ከሰል ለማቅረብ ተችሏል ብለዋል።

እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ በዘርፉ ለመሰማራት ፍቃድ ከወሰዱ ከ20 በላይ ማህበራት መካከል በአሁኑ ወቅት ወደምርት የገቡት ስምንት ብቻ ናቸው።

ይህም ዕቅዱ እንዳይሳካ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ በቀጣይ ዕቅዱን ለማሳካት ወደስራ ያልገቡትንና ፍቃድ ለመውሰድ በሂደት ላይ ያሉ ማህበራትን ወደ ስራ ለማስገባት ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።

የድንጋይ ከሰል ምርትን ጨምሮ ከማዕድን ዘርፍ በበጀት ዓመቱ ለሰባት ሺህ 717 ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ወደ 6 ሺህ የሚጠጉትን ተጠቃሚ ለማድረግ መቻሉንም አስታውቀዋል።

ዘርፉን ለማነቃቃት የተወሰደው እርምጃ ለዘመናት በሀብቱ ሳይጠቀም የቆየው የአካባቢው ነዋሪ ተጠቃሚ እንዲሆን እድል መፍጠሩን የገለጹት ድግሞ በክልሉ የዳውሮ ዞን ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ሀላፊ አቶ ሀይሌ ዱባለ ናቸው።


በተለይም በዞኑ የተቋቋመው የድንጋይ ከሰል ማበልፀጊያ ፋብሪካ ለበርካቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩንና ለአካባቢው ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ከፍተኛ መነቃቃት መፍጠሩንም ተናግረዋል ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቦንጋ ከተማ መካሄዱ የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026