
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 8/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው ሶስተኛው የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌዴሬሽን ጉባኤ እና አለም አቀፍ ኮንፈረንስ ተጠናቋል።
ከሚያዝያ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሲካሄድ የቆየው ሶስተኛው የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌደሬሽን ጉባኤና አለም አቀፍ ኮንፈረንስ የማጠቃለያ መርሃ-ግብር ተካሄዷል።
በማጠቃለያ መርሃ-ግብሩ ላይ የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ሐመድ አቡደል አሊም፣ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።
በሶስተኛው የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌዴሬሽን ጉባኤ እና አለም አቀፍ ኮንፈረንስ በአገራቱ መካከል የልምድ ልውውጥ የተደረገበት መሆኑ በዚሁ ወቅት ተገልጿል።
የአፍሪካ ዌልዲንግን በተመለከተ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት መደረጉም ታውቋል።
አፍሪካ በዌልዲንግ ዘርፍ ያላት ከፍተኛ አቅም የተዳሰሰ ሲሆን ሀገራት ዘርፉን ለማሳደግ በጋራ እንዲሰሩ ጥሪ የተደረገበት መሆኑ ተጠቁሟል።
ተሳታፊዎቹ በቆይታቸው ዓድዋ ድል መታሰቢያ እና አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከልን ጨምሮ የተለያዩ በከተማው የተሰሩ የልማት ስራዎችን መጎብኘታቸው ተገልጿል።
በዌልዲንግ ክህሎት ተወዳድረው አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎች ሽልማት ተበርክቷል።
አራተኛው የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌደሬሽን ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ እንደሚካሄድ ታውቋል።
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026