የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ተመድ ከኢትዮጵያ ጋር በዘላቂ ልማት እና እድገት ላይ ያለውን ትብብር እንደሚያጠናክር ገለጸ

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2017(ኢዜአ)፡- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከኢትዮጵያ ጋር በዘላቂ ልማት እና እድገት ላይ ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፕሮጀክት አገልግሎቶች ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር እና የተመድ ረዳት ዋና ፀሐፊ ሆርጌ ሞሬራ ዳ ሲልቫ ከገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ጋር ተወያይተዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ ከሚኒስትሩ ጋር ጽህፈት ቤቱ የኢትዮጵያን የልማት አጀንዳ መደገፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን የጽህፈት ቤቱ መረጃ ያመለክታል።

የመንግስት የግዢ ስርዓት እና የመልሶ መቋቋም ስራዎችን ጨምሮ ጽህፈት ቤቱ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ጽኑ እና የዘላቂ እድገት አጋርነት የበለጠ ለማጠናከር ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.