የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ ለትንሳኤ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት ግብረ ኃይል ተቋቁሙ እየተሰራ ነው

Apr 21, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፣ ሚያዚያ 10/2017 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለትንሳኤ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት ግብረ ኃይል ተቋቁሙ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮው ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠው ለኢዜአ እንደገለጹት ለትንሳኤ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰትና ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር ግብረሀይል ተቋቁሞ በቅንጅት እየተሰራ ነው።

የእንስሳት ተዋጽኦ፣ የአትክልትና የፋብሪካ ምርቶች ከአምራቹ ለሸማቹ በቀጥታ የሚደርስበት አሰራር መዘርጋቱን ገልጸው፣ ከሰንበት እስከ ሰንበት ገበያዎች ምርቶቹ በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ መቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡


በዚህም በክልሉ ለዞንና ለልዩ ወረዳዎች ከ224 ሺህ 300 በላይ ሊትር የምግብ ዘይት ለዞንና ለልዩ ወረዳዎች መሰራጨቱን አቶ ዳንኤል ገልጸዋል።

በገበያው የምርት እጥረትና ያልተገባ የዋጋ ጭማሪን ለመከላከልም ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ህብረተሰቡም ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ፣ ምርት ደብቀው የሚያከማቹና በምግብ ምርት ላይ ባዕድ ነገር ቀላቅለው የሚሸጡ ስግብግብ ነጋዴዎች ሲገጥሙት ለሚመለከተው የመንግስት አካል ፈጥኖ ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲያጠናክርም ጠይቀዋል።

በሆሳዕና ከተማ የአራዳ ቀበሌ ነዋሪ አቶ መኮንን ሻንቆ በሰጡት አስተያየት፣ በከተማው የበዓል ገበያው በአቅርቦትም ሆነ በዋጋ የተሻለ መሆኑን አንስተዋል።


በበዓል ገበያ የምርት የአቅርቦት እጥረት እንዳያጋጥም አስተዳደሩ እያደረገ ያለው የቁጥጥር ሥራ ሸማቹን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

በከተማው የሄጦ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ሊንረንሴ ዮሐንስ በበኩላቸው በከተማው በዋናው ገበያም ሆነ በሰንበት ገበያዎች ሁሉም የምርት ዓይነት መቅረቡንና እጥረት እንደሌለ ጠቁመው፣ "በገበያው እንደፍላጎታችን እየሸመትን ነው" ብለዋል።


ሽንኩርትን ጨምሮ ሌሎች ለበዓል የሚያስፈልጉ ምርቶች ላይ ከወትሮው የዋጋ ጭማሪ አለመኖሩ ገበያውን የተረጋጋ ማድረጉን ጠቅሰው፣ በገበያው ክትትልና ቁጥጥር መደረጉ ውጤት አምጥቷል፤ በቀጣይም ሊጠናከር ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026