የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ ለትንሳኤ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት ግብረ ኃይል ተቋቁሙ እየተሰራ ነው

Apr 21, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፣ ሚያዚያ 10/2017 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለትንሳኤ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት ግብረ ኃይል ተቋቁሙ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮው ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠው ለኢዜአ እንደገለጹት ለትንሳኤ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰትና ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር ግብረሀይል ተቋቁሞ በቅንጅት እየተሰራ ነው።

የእንስሳት ተዋጽኦ፣ የአትክልትና የፋብሪካ ምርቶች ከአምራቹ ለሸማቹ በቀጥታ የሚደርስበት አሰራር መዘርጋቱን ገልጸው፣ ከሰንበት እስከ ሰንበት ገበያዎች ምርቶቹ በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ መቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡


በዚህም በክልሉ ለዞንና ለልዩ ወረዳዎች ከ224 ሺህ 300 በላይ ሊትር የምግብ ዘይት ለዞንና ለልዩ ወረዳዎች መሰራጨቱን አቶ ዳንኤል ገልጸዋል።

በገበያው የምርት እጥረትና ያልተገባ የዋጋ ጭማሪን ለመከላከልም ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ህብረተሰቡም ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ፣ ምርት ደብቀው የሚያከማቹና በምግብ ምርት ላይ ባዕድ ነገር ቀላቅለው የሚሸጡ ስግብግብ ነጋዴዎች ሲገጥሙት ለሚመለከተው የመንግስት አካል ፈጥኖ ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲያጠናክርም ጠይቀዋል።

በሆሳዕና ከተማ የአራዳ ቀበሌ ነዋሪ አቶ መኮንን ሻንቆ በሰጡት አስተያየት፣ በከተማው የበዓል ገበያው በአቅርቦትም ሆነ በዋጋ የተሻለ መሆኑን አንስተዋል።


በበዓል ገበያ የምርት የአቅርቦት እጥረት እንዳያጋጥም አስተዳደሩ እያደረገ ያለው የቁጥጥር ሥራ ሸማቹን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

በከተማው የሄጦ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ሊንረንሴ ዮሐንስ በበኩላቸው በከተማው በዋናው ገበያም ሆነ በሰንበት ገበያዎች ሁሉም የምርት ዓይነት መቅረቡንና እጥረት እንደሌለ ጠቁመው፣ "በገበያው እንደፍላጎታችን እየሸመትን ነው" ብለዋል።


ሽንኩርትን ጨምሮ ሌሎች ለበዓል የሚያስፈልጉ ምርቶች ላይ ከወትሮው የዋጋ ጭማሪ አለመኖሩ ገበያውን የተረጋጋ ማድረጉን ጠቅሰው፣ በገበያው ክትትልና ቁጥጥር መደረጉ ውጤት አምጥቷል፤ በቀጣይም ሊጠናከር ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026