የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

አይኤምኤፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት አጠናክሮ ይቀጥላል- የድርጅቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር

Apr 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ ሚያዚያ 14/2017 (ኢዜአ)፡- ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ለኢትዮጵያ እድገት እና ልማት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የድርጅቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂዬቫ ገለጹ።

የዓለም ባንክ ግሩፕ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ ትናንት በዋሺንግተን ዲሲ ተጀምሯል።

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጂኦርጂዬቫ ከስብስባው ጎን ለጎን ከገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ እና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ጋር ተወያይተዋል።

ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ የኢትዮጵያን ሪፎርም አጀንዳ አስመልክቶ ውይይት ማድረጋቸውን በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።

አይኤምኤፍ የኢትዮጵያን እድገት እና ልማት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑንም አመልክተዋል።

የዓለም ባንክ ግሩፕ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ እስከ ሚያዚያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.