
አዲስ አበባ ፤ ሚያዚያ 14/2017 (ኢዜአ)፡- ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ለኢትዮጵያ እድገት እና ልማት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የድርጅቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂዬቫ ገለጹ።
የዓለም ባንክ ግሩፕ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ ትናንት በዋሺንግተን ዲሲ ተጀምሯል።
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጂኦርጂዬቫ ከስብስባው ጎን ለጎን ከገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ እና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ጋር ተወያይተዋል።
ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ የኢትዮጵያን ሪፎርም አጀንዳ አስመልክቶ ውይይት ማድረጋቸውን በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
አይኤምኤፍ የኢትዮጵያን እድገት እና ልማት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑንም አመልክተዋል።
የዓለም ባንክ ግሩፕ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ እስከ ሚያዚያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026