የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በደሴ ከተማ አስተዳደር ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የመንገድ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው

Apr 23, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ ሚያዚያ 14/2017 (ኢዜአ)፡-በደሴ ከተማ አስተዳደር ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የመንገድ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

የባለሰልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዷለም እሸቱ ለኢዜአ እንደገለጹት በከተማው የመንገድ ተደራሽነትን በማስፋት የከተማውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማቀላጠፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።


በዚህም በዘንድሮው ዓመት ብቻ የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ አራት ኪሎ ሜትር የመንገድ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

ከግንባታዎቹ መካከል ከመነሃሪያ አረብ ገንዳ መስጅድ አካባቢ የአንድ ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥና ከገብርኤል-ባህር ሺሽ-ቁርቁር አንድ ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ሥራዎች ይገኙበታል።


በተጨማሪም ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት-ወሎ ባህል አምባ እየተገነባ የሚገኘው ሁለት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እንደሚገኝበት ገልጸዋል።

ለመንገዶቹ ግንባታ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት መመደቡን ጠቁመው ሁሉም መንገዶች በተያዘው በጀት ዓመት መጨረሻ እንደሚጠናቀቁ አስታውቀዋል።

ለመንገዶቹ ግንባታም መንግስት ከመደበው በጀት በተጨማሪ ህብረተሰቡ በገንዘብ፣ በቁሳቁስና በጉልበቱ የራሱን አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።


የደሴ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሉባባ በሽር በበኩላቸው በከተማው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች እየተፋጠኑ በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የመንገዶቹ ግንባታ የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የሚመልሱ በመሆናቸው በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ በጥራት እንዲጠናቀቁ ነዋሪውም የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።


በከተማው ግንባታቸው በመከናወን ላይ ያሉ የአስፋልት መንገዶች የከተማውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንደሚያነቃቁ የገለጹት ደግሞ ሌላዋ የደሴ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ አባይነሽ ሀይሉ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026