የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በደሴ ከተማ አስተዳደር ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የመንገድ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው

Apr 23, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ ሚያዚያ 14/2017 (ኢዜአ)፡-በደሴ ከተማ አስተዳደር ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የመንገድ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

የባለሰልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዷለም እሸቱ ለኢዜአ እንደገለጹት በከተማው የመንገድ ተደራሽነትን በማስፋት የከተማውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማቀላጠፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።


በዚህም በዘንድሮው ዓመት ብቻ የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ አራት ኪሎ ሜትር የመንገድ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

ከግንባታዎቹ መካከል ከመነሃሪያ አረብ ገንዳ መስጅድ አካባቢ የአንድ ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥና ከገብርኤል-ባህር ሺሽ-ቁርቁር አንድ ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ሥራዎች ይገኙበታል።


በተጨማሪም ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት-ወሎ ባህል አምባ እየተገነባ የሚገኘው ሁለት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እንደሚገኝበት ገልጸዋል።

ለመንገዶቹ ግንባታ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት መመደቡን ጠቁመው ሁሉም መንገዶች በተያዘው በጀት ዓመት መጨረሻ እንደሚጠናቀቁ አስታውቀዋል።

ለመንገዶቹ ግንባታም መንግስት ከመደበው በጀት በተጨማሪ ህብረተሰቡ በገንዘብ፣ በቁሳቁስና በጉልበቱ የራሱን አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።


የደሴ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሉባባ በሽር በበኩላቸው በከተማው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች እየተፋጠኑ በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የመንገዶቹ ግንባታ የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የሚመልሱ በመሆናቸው በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ በጥራት እንዲጠናቀቁ ነዋሪውም የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።


በከተማው ግንባታቸው በመከናወን ላይ ያሉ የአስፋልት መንገዶች የከተማውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንደሚያነቃቁ የገለጹት ደግሞ ሌላዋ የደሴ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ አባይነሽ ሀይሉ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026