የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በደሴ ከተማ አስተዳደር ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የመንገድ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው

Apr 23, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ ሚያዚያ 14/2017 (ኢዜአ)፡-በደሴ ከተማ አስተዳደር ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የመንገድ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

የባለሰልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዷለም እሸቱ ለኢዜአ እንደገለጹት በከተማው የመንገድ ተደራሽነትን በማስፋት የከተማውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማቀላጠፍ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።


በዚህም በዘንድሮው ዓመት ብቻ የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ አራት ኪሎ ሜትር የመንገድ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

ከግንባታዎቹ መካከል ከመነሃሪያ አረብ ገንዳ መስጅድ አካባቢ የአንድ ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥና ከገብርኤል-ባህር ሺሽ-ቁርቁር አንድ ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ሥራዎች ይገኙበታል።


በተጨማሪም ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት-ወሎ ባህል አምባ እየተገነባ የሚገኘው ሁለት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እንደሚገኝበት ገልጸዋል።

ለመንገዶቹ ግንባታ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት መመደቡን ጠቁመው ሁሉም መንገዶች በተያዘው በጀት ዓመት መጨረሻ እንደሚጠናቀቁ አስታውቀዋል።

ለመንገዶቹ ግንባታም መንግስት ከመደበው በጀት በተጨማሪ ህብረተሰቡ በገንዘብ፣ በቁሳቁስና በጉልበቱ የራሱን አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።


የደሴ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሉባባ በሽር በበኩላቸው በከተማው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች እየተፋጠኑ በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የመንገዶቹ ግንባታ የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የሚመልሱ በመሆናቸው በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ በጥራት እንዲጠናቀቁ ነዋሪውም የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።


በከተማው ግንባታቸው በመከናወን ላይ ያሉ የአስፋልት መንገዶች የከተማውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንደሚያነቃቁ የገለጹት ደግሞ ሌላዋ የደሴ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ አባይነሽ ሀይሉ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026