የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

እስካሁን ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር ላይ የደረሰ የበጋ መስኖ ስንዴ ምርት ተሰብስቧል-ግብርና ሚኒስቴር

Apr 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፦በዘንድሮ የበጋ መስኖ ስንዴ ከለማው ሰብል እስካሁን ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የደረሰ ምርት መሰብሰቡን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።


በሌላ በኩል በበልግ ወቅት 98 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማምረት እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል።


በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ኢሳያስ ለማ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አርሶ አደሮች በመኸር፣ በበልግና በበጋ መስኖ ዓመቱን ሙሉ እንዲያመርቱ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡


ሳይታረሱ የቆዩ መሬቶችን ወደ ልማት በማስገባት በዘር የሚሸፈን የመሬት መጠንን መጨመር፣የግብርና ቴክኖሎጂ፣ግብዓትና ምርጥ ዘሮችን መጠቀም ለምርትና ምርታማነት መጨመር ምክንያት መሆናችውን አመላክተዋል፡፡


በበጋ መስኖ ልማት የተጀመሩ ሥራዎችም አርሶ አደሩ በዓመት በሶስት ዙር እንዲያመርት በማድረግ ከፍተኛ ምርት እያስገኙ ናቸው ብለዋል።


በዚህ ዓመት ከበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 172 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማምረት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ጠቅሰዋል።


እስካሁን ሶስት ነጥብ አምስት ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የገለጹት አቶ ኢሳያስ፥ ቀደም ብሎ የተዘራ እና የደረሰ የበጋ መስኖ ስንዴ ምርት እየተሰበሰበ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።


በዚህም እስካሁን በ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የደረሰ ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል።


በሌላ በኩል ወቅቱ የበልግ ሰብል ልማት የሚከናወንበት መሆኑን ጠቅሰው፥ በበልግ አብቃይ አካባቢዎች በስፋት ወደ ሥራ መገባቱን ተናግረዋል፡፡


በዚህም በዘንድሮ በልግ ሶስት ነጥብ ሰባት ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር በመሸፈን 98 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማምረት መታቀዱን ጠቅሰው፥ እስካሁን 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ገልጸዋል፡፡


አርሶ አደሮች በቀሪ የበልግ ወቅት በዘር ያልተሸፈነ መሬታቸውን በመሸፈን ቀድሞ በዘር የተሸፈነውን የአረም ቁጥጥርና ተባይ ክትትል እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026