የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

እስካሁን ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር ላይ የደረሰ የበጋ መስኖ ስንዴ ምርት ተሰብስቧል-ግብርና ሚኒስቴር

Apr 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፦በዘንድሮ የበጋ መስኖ ስንዴ ከለማው ሰብል እስካሁን ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የደረሰ ምርት መሰብሰቡን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።


በሌላ በኩል በበልግ ወቅት 98 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማምረት እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል።


በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ኢሳያስ ለማ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አርሶ አደሮች በመኸር፣ በበልግና በበጋ መስኖ ዓመቱን ሙሉ እንዲያመርቱ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡


ሳይታረሱ የቆዩ መሬቶችን ወደ ልማት በማስገባት በዘር የሚሸፈን የመሬት መጠንን መጨመር፣የግብርና ቴክኖሎጂ፣ግብዓትና ምርጥ ዘሮችን መጠቀም ለምርትና ምርታማነት መጨመር ምክንያት መሆናችውን አመላክተዋል፡፡


በበጋ መስኖ ልማት የተጀመሩ ሥራዎችም አርሶ አደሩ በዓመት በሶስት ዙር እንዲያመርት በማድረግ ከፍተኛ ምርት እያስገኙ ናቸው ብለዋል።


በዚህ ዓመት ከበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 172 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማምረት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ጠቅሰዋል።


እስካሁን ሶስት ነጥብ አምስት ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የገለጹት አቶ ኢሳያስ፥ ቀደም ብሎ የተዘራ እና የደረሰ የበጋ መስኖ ስንዴ ምርት እየተሰበሰበ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።


በዚህም እስካሁን በ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ የደረሰ ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል።


በሌላ በኩል ወቅቱ የበልግ ሰብል ልማት የሚከናወንበት መሆኑን ጠቅሰው፥ በበልግ አብቃይ አካባቢዎች በስፋት ወደ ሥራ መገባቱን ተናግረዋል፡፡


በዚህም በዘንድሮ በልግ ሶስት ነጥብ ሰባት ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር በመሸፈን 98 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማምረት መታቀዱን ጠቅሰው፥ እስካሁን 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ገልጸዋል፡፡


አርሶ አደሮች በቀሪ የበልግ ወቅት በዘር ያልተሸፈነ መሬታቸውን በመሸፈን ቀድሞ በዘር የተሸፈነውን የአረም ቁጥጥርና ተባይ ክትትል እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026