የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በሀረሪ ክልል የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች በተቀናጀ መንገድ ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ርዕሰ መስተደድር ኦርዲን በድሪ

Apr 24, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ሚያዚያ 15/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ዘላቂ ሰላምና የህግ የበላይነትን በማጠናከር የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች በተቀናጀ መንገድ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተደድር ኦርዲን በድሪ አስታወቁ።

ለሁለት ቀናት የተካሄደው የክልሉ የ2017 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ ማምሻውን ተጠናቋል።


አቶ ኦርዲን በድሪ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ በዘንድሮ በጀት አመት ዘጠኝ ወራት የገጠርና የከተማውን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ አበረታች ልማቶች ተከናውነዋል።

በሌሎችም በማህበራዊ፣ በምጣኔ ሃብት እንዲሁም በሰላምና መልካም አስተዳደር ዘርፎች የህዝቡን መሠረታዊ ጥያቄዎች የመለሱ ተግባራት መከናወናቸውን አመልክተዋል።

በቀጣይም የተገኙ ውጤቶችን በማስፋት ብዙ መትጋትና መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።

በተለይም ዘላቂ ሰላምና የህግ የበላይነትን በማጠናከር የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በፍትህና በፀጥታ ተቋማት የተጀመሩ አበረታች የሪፎርም ስራዎች በተቀናጀ መንገድ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።

ሴክተሮች የተቀናጀና የተናበበ ስራዎችን በላቀ ደረጃ በመፈፀም፤ ብልሹ አሠራሮችና ሌብነትን በመታገል የህብረተሰቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በላቀ ደረጃ እንዲመለሱ በቀሪ ወራት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በገቢ አሰባሰብ፣ በልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸምና በቱሪዝም ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን አመላክተዋል።

በውይይቱ የተሳተፉ በየደረጃው ያሉ አመራሮችም በቀጣይ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚተጉ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026