የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የዓለም የአብራሪዎች ቀን እየተከበረ ነው

Apr 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 18/2017(ኢዜአ)፦ዓለም አቀፉ የአብራሪዎች ቀን (World Pilots’ Day) ዛሬ እየተከበረ ይገኛል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መልዕክት የዛሬው ቀን የአየር መንገዱ የስኬት እና የጀግንነት ተምሳሌት ለሆኑት አብራሪዎች ክብር የምንሰጠበት ነው ብሏል።

አብራሪዎች በክህሎታቸው፣ በታታሪነታቸው እና በጠንካራ የጸና መንፈስ የአፍሪካን ህልሞች ወደ ተለያዩ የዓለም ክፍሎች ይዞ በመጓዝ ሀገራትን፣ ባህሎች እና እድሎችን በማስተሳሰር ቁልፍ ሚና እየተወጡ ነው ብሏል።

ዛሬም ሁልጊዜም እናከብራችኋለን ሲል ገልጿል አየር መንገዱ ባስተላለፈው መልዕክት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.