የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኮደርስ ስልጠና በዲጅታል ዘርፍ የኢትዮጵያን የምጣኔ ሃብት እድገት ለማሳለጥ ፋይዳው የላቀ ነው

May 6, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ሚያዚያ 24/2017 (ኢዜአ)፦የኮደርስ ስልጠና በዲጅታል ዘርፍ የኢትዮጵያን የምጣኔ ሃብት እድገት ለማሳለጥና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ፋይዳው የላቀ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተሞች ልማት ክላስተር አስተባባሪና የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ገለጹ።


በአማራ ክልል በዘጠኝ ወራት የተከናወኑ የኮደርስ ስልጠና አፈጻጸም በተመለከተ በደሴ ከተማ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።


አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፥ የኮደርስ ስልጠና በዲጅታል ዘርፍ የኢትዮጵያን የምጣኔ ሃብት እድገት ለማሳለጥና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ፋይዳው የላቀ ነው።


ለዚህም መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አንስተው፥ በተለይም ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እድል ተጠቃሚ ለመሆን መትጋት አለባቸው ብለዋል።


የኮደርስ ስልጠና በእውቀት እና ክህሎት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርግ በመሆኑ አጋጣሚው እንዳያመልጥ ሁሉም ሊሰለጥን እንደሚገባም አንስተዋል።


በመሆኑም በቀጣይ በተለይም ወጣቶች ስልጠናው ሊያመልጣቸው እንደማይገባ አንስተው፥በተለይ ዩኒቨርሲቲዎችና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የስልጠና ክፍል በማዘጋጀትና ግብዓት በማሟላት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።


የአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ የቻለ ይግዛው፥የኮደርስ ስልጠና በቴክኖሎጂ የዳበረ ትውልድ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።


በዚህም በክልሉ ስልጠናውን በማጠናከር ቴክኖሎጂን፣ክህሎትንና ዘመናዊ አሰራሮችን ለማስፋፋትና ለማሻሻል በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።


በበጀት ዓመቱ ከ192 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች ስልጠናውን እንዲወስዱ ታቅዶ እስካሁን ከ100 ሺህ በላይ ዜጎች መሰልጠናቸውን ተናግረዋል።


በመድረኩ የክልል፣የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026