የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) የወራቤ ከተማን የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ሥራ አስጀመሩ

May 7, 2025

IDOPRESS

ወራቤ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ የ5 ነጥብ 72 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ሥራ አስጀመሩ።

ለመንገዱ ዛሬ የመሰረት ድንጋይ ተቀምጦ ስራው በተጀመረበት ወቅት እንደተገለጸው የአስፓልት መንገዱ ከ1 ቢሊዮን 61 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቅ ነው።

የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ወጪ በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ እንደሚሸፈንም ተመልክቷል፡፡

ፕሮጀክቱ በሁለት ዓመት ከ3 ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃም ተገልጿል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ የመንገዱን ግንባታ ሥራ ከማስጀመር በተጨማሪ በዞኑ ዳሎቻ ከተማ አስተዳደር በ194 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባውን የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል፡፡

የውሃ ፕሮጀክቱ ከ33ሺህ በላይ የአካባቢውን የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ያደርጋልም ተብሏል።

በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የፌዴራል፣ የክልሉና የስልጤ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026