የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) የወራቤ ከተማን የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ሥራ አስጀመሩ

May 7, 2025

IDOPRESS

ወራቤ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ የ5 ነጥብ 72 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ሥራ አስጀመሩ።

ለመንገዱ ዛሬ የመሰረት ድንጋይ ተቀምጦ ስራው በተጀመረበት ወቅት እንደተገለጸው የአስፓልት መንገዱ ከ1 ቢሊዮን 61 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቅ ነው።

የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ወጪ በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ እንደሚሸፈንም ተመልክቷል፡፡

ፕሮጀክቱ በሁለት ዓመት ከ3 ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃም ተገልጿል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ የመንገዱን ግንባታ ሥራ ከማስጀመር በተጨማሪ በዞኑ ዳሎቻ ከተማ አስተዳደር በ194 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባውን የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል፡፡

የውሃ ፕሮጀክቱ ከ33ሺህ በላይ የአካባቢውን የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ያደርጋልም ተብሏል።

በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የፌዴራል፣ የክልሉና የስልጤ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.