
ወራቤ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ የ5 ነጥብ 72 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ሥራ አስጀመሩ።
ለመንገዱ ዛሬ የመሰረት ድንጋይ ተቀምጦ ስራው በተጀመረበት ወቅት እንደተገለጸው የአስፓልት መንገዱ ከ1 ቢሊዮን 61 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቅ ነው።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ወጪ በመንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ እንደሚሸፈንም ተመልክቷል፡፡
ፕሮጀክቱ በሁለት ዓመት ከ3 ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃም ተገልጿል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ የመንገዱን ግንባታ ሥራ ከማስጀመር በተጨማሪ በዞኑ ዳሎቻ ከተማ አስተዳደር በ194 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባውን የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል፡፡
የውሃ ፕሮጀክቱ ከ33ሺህ በላይ የአካባቢውን የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ያደርጋልም ተብሏል።
በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የፌዴራል፣ የክልሉና የስልጤ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026