የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአፋር ክልል የአርብቶ አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

May 12, 2025

IDOPRESS

ሰመራ፤ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል የአርብቶ አደሩ የኑሮ መሰረት የሆኑ እንስሳትን በመንከባከብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን የማጎልበት ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸው ተገልጿል።


በክልሉ ጭፍራ ወረዳ የተገነቡ የተለያዩ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችና የመኖ ልማት ስራዎች የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት በተገኙበት ዛሬ ተመርቀዋል።


በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፥ በክልሉ የአርብቶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተግባራት ናቸው።


በዚህም የአርብቶ አደሩ የኑሮ መሰረት የሆኑ እንስሳትን በመንከባከብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ ከሚያስችሉ ተግባራት መካከል የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችና የእንስሳት መኖ ልማት ስራዎች ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።


ለእንሰሳቱ የሚደረገው ድጋፍና እንክብካቤም የአርብቶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንደሚያጠናክርም አስረድተዋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመሬት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ዑመር ኑሩ እንደተናገሩት በክልሉ ድርቅን ለመቋቋም የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ ነው።


በተለይም የአርብቶ አደሩን ተጋላጭነት ለመቀነስና ኑሮውን ለማሻሻል ከተሰሩ ፕሮጀክቶች መካከል በጭፍራ ወረዳ ላይ ተገንብተው ለምረቃ የበቁት የውሃና የመኖ ልማት ስራዎች ለአብነት እንደሚጠቀሱም ተናግረዋል።


በክልሉ አራት ወረዳዎች በተከናወኑ የልማት ተግባራት የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የገለፁት ደግሞ የክልሉ የእንስሳትና ዓሣ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም መሐመድ ናቸው።


የጭፍራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አሊ አርባ በበኩላቸው፥ ከለውጥ በኃላ በተሰሩ ስራዎች አርብቶ አደሩ ማህበረሰብን ደረጃ በደረጃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አመልክተዋል።


አስተዳዳሪው አክለውም ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል በወረዳቸው ከሚገኝ ወንዝ በፀሐይ ኃይል በመታገዝ ውሃን በመጥለፍ የተከናወነው የእንስሳት መኖ ልማት ሊጠቀስ እንደሚችል ገልፀዋል።


በክልሉ በሚገኙ ደዌ፣ ተላላክ፣ አሚባራና ጭፍራ ወረዳዎች የተለያዩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን ዛሬ ለምረቃ የበቁት በጭፍራ ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች የተጠናቀቁት መሆናቸውም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026