
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) ገለጹ።
ኮሚሽነሩ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት፥ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት እምቅ ሀብቶች የማስተዋወቅ ስራ በስፋት ሲሰራ ቆይቷል።
ኢንቨስት ሊደረግባቸው የሚችሉ ዘርፎችን በማስተዋወቅ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ በተሰራ ስራ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡንም ተናግረዋል።
በዘርፉ የተሻሻሉ ህጎች፣ አዋጆችና ደንቦች እንዲሁም የመንግስት ቁርጠኝነት ከፍተኛ ለውጥ እያመጡ መሆኑን ገልጸዋል።

መንግስት ትኩረት በሰጠባቸው የግብርና፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አይሲቲ ዘርፎች በርካታ ባለሀብቶች መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ እየተሰራ ነው ብለዋል።
እንደኮሚሽነሩ ገለፃ የገቢና ወጪ ንግድ እንዲሁም የጅምላና ችርቻሮ ንግዱ ለውጭ ባለሀብቶች መከፈቱ ትልቅ ዕድል ፈጭሯል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፈተናዎችን በመቋቋም እያንሰራራ እንደሚገኝም ኮሚሽነር ዘለቀ(ዶ/ር) ጨምረው ተናግረዋል።

በተለይም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መልካም ዕድል የፈጠረና እድገት እንዲመዘገብ ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች በተለያዩ መስኮች ኢንቨስት እያደረጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለሚያደርጉ ባለሃብቶች የመንግስት ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...
Jun 9, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...
May 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...
Apr 20, 2026