
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) ገለጹ።
ኮሚሽነሩ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት፥ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት እምቅ ሀብቶች የማስተዋወቅ ስራ በስፋት ሲሰራ ቆይቷል።
ኢንቨስት ሊደረግባቸው የሚችሉ ዘርፎችን በማስተዋወቅ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ በተሰራ ስራ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡንም ተናግረዋል።
በዘርፉ የተሻሻሉ ህጎች፣ አዋጆችና ደንቦች እንዲሁም የመንግስት ቁርጠኝነት ከፍተኛ ለውጥ እያመጡ መሆኑን ገልጸዋል።

መንግስት ትኩረት በሰጠባቸው የግብርና፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም፣ ማኑፋክቸሪንግ እና አይሲቲ ዘርፎች በርካታ ባለሀብቶች መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ እየተሰራ ነው ብለዋል።
እንደኮሚሽነሩ ገለፃ የገቢና ወጪ ንግድ እንዲሁም የጅምላና ችርቻሮ ንግዱ ለውጭ ባለሀብቶች መከፈቱ ትልቅ ዕድል ፈጭሯል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፈተናዎችን በመቋቋም እያንሰራራ እንደሚገኝም ኮሚሽነር ዘለቀ(ዶ/ር) ጨምረው ተናግረዋል።

በተለይም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መልካም ዕድል የፈጠረና እድገት እንዲመዘገብ ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች በተለያዩ መስኮች ኢንቨስት እያደረጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለሚያደርጉ ባለሃብቶች የመንግስት ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026