የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የህዝብን ችግር በዘላቂነት የሚፈቱ ናቸው - ነዋሪዎች

May 15, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና ፡ ግንቦት 6/2017 (ኢዜአ)፡-.በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በተለያዩ አካባቢዎች የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የህዝብን ችግር በዘላቂነት የሚፈቱ በመሆናቸው ሊጠናከሩ እንደሚገባ አስተያየታቸውን የሰጡ የክልሉ ነዋሪዎች ገለጹ ፡፡

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ግንባታቸው እየተከናወኑ ከሚገኙ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የተጠናቀቁትን መርቀው አገልግሎት እያስጀመሩ ይገኛሉ፡፡

ነዋሪዎቹ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በአካባቢያቸው የተገነቡት የመንገድ፣ የውሃና ሌሎች የመሰረተ ልማት ስራዎች የነዋሪውን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ናቸው።

በክልሉ በምስራቅ ጉራጌ ዞን ደቡብ ሶዶ ወረዳ ሜልኮ ኩሉንዴ ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሮ ትዕግስት አየለ እንዳሉት አገልግሎት መስጠት የጀመረው የሜልኮ ጉምባርናዳ መንገድ ከዚህ ቀደም የነበረባቸውን ዘርፈ ብዙ ችግር የፈታ ነው።


ከሰሞኑ ተመርቆ ወደ አገልግሎት ከገቡት ውስጥ በሀዲያ ዞን አን ሌሞ ወረዳ የተገነባው የ15 ኪሎ ሜትር የገጠር መንገድ አንዱ ሲሆን በወረዳው የከቤቾ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ተማም ፉሉሴ የመንገድ ግንባታው ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገልፀዋል፡፡

በስልጤ ዞን የዳሎቻ ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ በይዳ ሁሴን በበኩላቸው በንጹህ መጠጥ ውሃ እጥረት ሳቢያ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ሲዳረጉ መቆየታቸውን አስታውሰው አሁን ችግሮቹ እንደተፈቱም ገልፀዋል፡፡


መንግስት በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች እያከናወናቸው የሚገኙ የመሰረተ ልማት ስራዎችን አጠናክሮ እንዲቀጥል የጠየቁት ነዋሪዎቹ የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር ለመፍታት እየተደረገ ያለውን ጥረት ለማገዝ ቁርጠኛ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በበኩላቸው በክልሉ የህዝብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግና ፈጣን ዕድገትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል፡፡


ግብርናን ለማሳለጥ የሚያስችሉ የመስኖ አውታሮች፣ በክልሉ ክላስተር ማዕከላት 165 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት፣ የጤና ተቋማትና የማህበረሰብ መድኃኒት ቤቶችን አካቶ 90 የተለያዩ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑንም አክለዋል፡፡

የክልሉ መንግሥት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅሰው ነዋሪዎች የልማት ስራዎችን በመደገፍና በጥንቃቄ በመጠቀም ፈጣን እድገት እንዲረጋገጥ አስተዋጽኦ ማበርከት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል ፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026