
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት የለውጥ አመታት አዲስ አበባ ከተማን ለማስዋብ እና የትምህርት ቤቶችን አቅም ለማሻሻል የተከናወኑ ተግባራት የሚደነቁ መሆናቸውን መምህራንና የትምህርት አመራሮች ገለጹ፡፡
ከአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ መምህራንና የትምህርት አመራር አባላት በመዲናዋ የተከናወኑ እና እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
ኢዜአ ካነጋገራቸው መካከል የወርሃ የካቲት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር በለጠ መኮንን፤ አዲስ አበባ ከተማ እንደ ስሟ ውብ ሆናለች ብለዋል፡፡
በጉብኝቱ በመዲናዋ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ሁሉ ሰው ተኮር መሆናቸውን በተግባር አረጋግጫለሁ ነው ያሉት፡፡
በተለይ በመንገድ፣ በመብራት፣ በመዝናኛና ሌሎች መሰረተ ልማቶች እንዲሁም በትምህርት ቤቶች የተደረጉ የማሻሻያ እርምጃዎች ይበል የሚያስብሉ ናቸው ብለዋል፡፡
የጠመንጃ ያዥ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ደሳለኝ ታዬ እንደገለጹት፤ የትምህርት ቤቶችን የመማር ማስተማር ስራ ምቹ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት አስደማሚ ናቸው፡፡
ትምህርት ቤቶች ላይ የተሰሩ ስራዎች ሁለንተናዊ ስብዕናው የተሟላ ትውልድ ከመገንባት አኳያ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበርክታሉ ነው ያሉት፡፡
የአዲስ ምዕራፍ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርዕሰ መምህር መዓዛ አበጋዝ፤ ካዛንችስ እንዳደጉ እና አካባቢው ለመኖር እጅግ አስቸጋሪ እንደነበር አውስተዋል፡፡
በአጭር ጊዜ ውስጥ አምሮ እና ተውቦ በማየታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው፤ ጉዳት እንዳይደርስበት ሁላችንም ልንጠብቀው ይገባል ብለዋል፡፡
የአዲስ ምዕራፍ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህርት ኢፍቱ ኢብራሔም፤ በጉብኝቱ ወቅት ለትውልድ የሚሻገሩና በቀጣይም ተጠናክረው መቀጠል ያለባቸው የልማት ስራዎችን አይቻለሁ ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዘላለም ሙላቱ(ዶ/ር)፤ የጉብኝቱ ዓላማ መንግስት እያከናወናቸው ያሉ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ የልማት ተግባራትን በተመለከተ በቂ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው ብለዋል፡፡
በለውጥ ዓመታት አዲስ አበባን ውብና ጽዱ ከማድረግ በተጨማሪ የትምህርት ስብራቱን ለማከም በተወሰዱ እርምጃዎች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
መንግስት ከሚወስዳቸው የትምህርት ቤት ማሻሻያ እርምጃዎች በተጨማሪ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ከ10 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ በሚሆን ወጪ የትምህርት ቤት ማሻሻያ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026