የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ለማፋጠን ርብርብ እየተደረገ ነው-ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ

May 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ በማፋጠን ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ።


ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የኢትዮጵያን ቴክኖሎጂ ኤክስፖ ETEX 2025 በይፋ ከፍተዋል።


በዚሁ ወቅት ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂን ለዘላቂ ልማት፣ለኢኮኖሚና ለማህበራዊ ብልጽግና ለመጠቀም በቁርጠኝነት እየሰራች ነው ብለዋል።


ኤክስፖው የቴክኖሎጂ ዕድገትን ከማሳየት ባለፈ የተለያዩ ሀሳቦች የሚንሸራሸሩበትና ትብብር የሚጠናከርበት መሆኑንም አንስተዋል።


ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂን ያማከለ ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ ስትራቴጂ ነድፋ የተለያዩ ስራዎች እየሰራች መሆኑንም አንስተዋል።


ባለፉት ጥቂት ዓመታት በቴክኖሎጂ ልማት የተከናወኑ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑንም ገልጸዋል።


ኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎትን በተለያዩ ዘርፎች ላይ በመጠቀም ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ እየሰራች መሆኑንም ነው ያነሱት።


ለአብነትም በግብርናና በጤና ዘርፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግና የጤና አገልግሎትን ማዘመን መቻሉን አንስተዋል።


ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን የማድረጉ አንዱ ማሳያ ስማርት ሲቲ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህንም የዜጎችን ኑሮ በማቃለል ዘመናዊነትን እያላበሰ ነው ብለዋል።


ወጣቶች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ በስፋት የሚሳተፉበት የ5 ሚሊዮን ኮደርስን ጨምሮ የተለያዩ ስልጠናዎችን እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ እውን ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ነውም ብለዋል።


ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 እውን ለማድረግ የወጣቶችን ተሳትፎ በትምህርትና ስልጠና የበለጠ ማሳደግ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።


የቴክኖሎጂ ኤክስፖው እስከ ግንቦት 10/2017 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የበርካታ ሀገራት ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችና ከአስር ሺህ በላይ ተሳታፊዎች እየተሳተፉበት ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.