የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የመኸር እርሻውን በኩታ ገጠም ዘዴና በቴክኖሎጂ ታግዘን በማሳ ዝግጅት ላይ ነን -አርሶ አደሮች

May 19, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦የመኸር እርሻውን በኩታገጠም ዘዴና በቴክኖሎጂ ታግዘው ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአቡራሞ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመኸር እርሻ ዝግጅቱ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የገለጸው ደግሞ የክልሉ ግብርና ቢሮ ነው።


በክልሉ አቡራሞ ወረዳ ማሳቸውን በትራክተር ሲያርሱ ያገኘናቸው አርሶ አደር ፈይሰል ኑረይን፥ ለመኸር እርሻው 20 ሄክታር የሚሆን ማሳ ለዘር ማዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።


የኩታ ገጠም እርሻ ምርታማነትን ለማሳደግና ሰብልን በጋራ ለመንከባከብ ያግዛል ያሉት አርሶ አደሩ፤ለሌሎች አርሶ አደሮችም ተሞክሯቸውን እያጋሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።


ሌላው አርሶ አደር ፋንታሁን እጅጉ በበኩላቸው፥ 60 ሄክታር ማሳ ለማልማት ዝግጅታቸውን በማጠናቀቅ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በወረዳው በእስካአሁኑ እንቅስቃሴ 63 ሺህ ሄክታር ማሳ ለዘር የተዘጋጀ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የአቡራሞ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አታላይ ደረጀ ናቸው።


ከዚህ ውስጥ 53 ሺህ ሄክታር የሚሆነው ማሳ በኩታ ገጠም የሚለማ መሆኑን ገልጸው፤አርሶ አደሩን ከባህላዊ አስተራረስ በማላቀቅ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን እንዲላመድ በመድረጉ ምርታማነቱ እንዲጨምር ማድረጉን ጠቁመዋል።


አርሶ አደሩ የግብዓት አቅርቦት እንዲያገኝ በቂ ዝግጅት መደረጉን አስታውሰው፥ በተለይም በዘር ብዜት ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።


በክልሉ ግብርና ቢሮ የኤክስቴንሽን፣ግብዓት ስርጭትና አቅርቦት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ተሰማ እንደተናገሩት፥ በዘንድሮው የመኸር እርሻ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር ማሳ በዘር ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።


በአሁኑ ወቅትም የማሳ ዝግጅቱ ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመው፥ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምና የኩታ ገጠም አስተራረስ ተመራጭ በመሆኑ አርሶአደሩ ተግባራዊ እያደረገው ነው ብለዋል።


አርሶአደሩ በትራክተር እያረሰ ነው ያሉት አቶ ፀጋዬ፣ይህም የእርሻ ማሳን ለማስፋፋት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ልምዳቸውን ያሳድገዋል ነው ያሉት።


ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ለአርሶአደሩ እና አልሚ ባለሃብቶች የማዳበሪያ እና የምርጥ ዘር ስርጭት እየተከናወነ እንደሆነ ገልጸዋል።


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ 55 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ትግበራ ተገብቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026