
ድሬደዋ፣ግንቦት 16/2017(ኢዜአ)፦የባቡር መሠረተ ልማቱን ደህንነት በመጠበቅ የተሳካ አገልግሎት እንዲሰጥ ተቀናጅተው እንደሚሰሩ የሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን እና የድሬደዋ አስተዳደር የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ።
የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክስዮን ማህበር የባቡር ደህንነትን ለመጠበቅ የሚያስችል ውይይት ከሲቲ ዞንና ከድሬደዋ አስተዳደር የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ዛሬ ውይይት አካሂዷል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉት ኡጋዞች፣ የአገር ሽማግሌዎች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የባቡር መሠረተ ልማትና ደህንነት በመጠበቅ የተሳካ አገልግሎት እንዲሰጥ ተቀናጀተው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
የሶማሌ ኢሳ ማህበረሰብ ኡጋዝ ተወካይ አቶ አብዶ ኡመር ለኢዜአ እንደገለፁት፥ ባቡር የአገራችን የወጭና ገቢ ንግድ ማመላለሻና የብልፅግና ማሳኪያ አውታር ነው።
በተጨማሪም ለሲቲ ዞን ሁለንተናዊ ዕድገትና ለአካባቢው ወጣቶች የስራ ዕድል እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
ባቡሩ በሚያልፍበት የሲቲ ዞን ከእንስሳትና ከሰው ጋር በተያያዘ የሚገጥሙትን አደጋዎችና የፀጥታ ችግሮች በተደራጀ እና በተቀናጀ መንገድ እንከላከላለን ብለዋል።
አጋዝ አብዱረዛቅ አጋዝ አሊ በበኩላቸው፥ የሚመሩትን የህብረተሰብ ክፍል በማስተባበር የባቡር መሠረተ ልማትና የሚጓዝበትን መስመሮች እየጠበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የባቡር መሠረተ ልማት የህልውናችን ጉዳይ በመሆኑ እኛ የአገር ሽማግሌዎች መስመሩን በተቀናጀ መንገድ መጠበቅ ይገባናል ያሉት የድሬደዋ የአገር ሽማግሌና አባገዳ አቶ ጉይሳ ኢብሳ ናቸው።
ለባቡሩ ደህንነት የወጣውን መመሪያ በአግባቡ በመተግበር ባቡሩን ከእንሰሳትና ከሰው ንክኪ መጠበቅ እንደሚገባም አመልክተዋል።
የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክስዮን ማህበር የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ወይዘሮ ሙና አህመድ በበኩላቸው፥ የባቡር መስመሩ በሚያልፍባቸው ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር የተካሄደው ውይይት የባቡር ትራንስፖርት ደህንነትና ሰላማዊ ጉዞ ይበልጥ የሚያጠናክር ነው ብለዋል።
የድሬደዋና የሲቲ ዞን የህብረተሰብ ክፍሎች የባቡርን ጥቅም የሚረዱና በመሆናቸው ባቡሩ በምንም አይነት ሰው ሰራሽ ችግሮች እንዳይስተጓጎል እያደረጉ የሚገኙትን አስተዋጽኦ እንዲያጠናክሩ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የወጣውን የባቡር ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብን ህብረተሰቡ በአግባቡ እንዲረዳ ማሳወቅ መቻሉን ገልጸዋል።
በውይይቱ ላይ የኃይማኖት አባቶች፣ኡጋዞች፣የአገር ሽማግሌዎች፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የሲቲ ዞንና የድሬዳዋ አስተዳደር አመራሮች እና የፀጥታ አካላት ተሳትፈዋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026