
ደብረ ብርሃን፤ ግንቦት 17/2017(ኢዜአ)፦ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የታየው መነቃቃት የሀገርን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ መሰረት የሚያኖር መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ክላስተር አስተባባሪና የአማራ ክልል የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ አህመዲን መሐመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
በክልል ደረጃ "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ የንቅናቄ መድረክ በደብረ ብርሃን ከተማ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ክላስተር አስተባባሪና የአማራ ክልል የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ አህመዲን መሐመድ(ዶ/ር)፤ በሀገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በሁሉም ዘርፎች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን አንስተው በተለይም በአምራች ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃት እየተፈጠረ ይገኛል ብለዋል።
በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝምና ሌሎችም ዘርፎች የተመዘገበው ስኬት ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ መሆኑን አንስተው የዘርፉ መነቃቃት ከውጭ የሚገባውን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት እያስቻለ ነው ብለዋል።
በመሆኑም በኬሚካል፣ በብረታብረት፣ በመድሃኒትና ሌሎች ኢንዱስትሪዎች እድገትና ብልጽግና ለማምጣት እንደሀገር የተያዘውን ግብ ለማሳካት ቅንጅታዊ ስራዎች እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
ለዚህም በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሃብቶች ድጋፍ እንደሚደረግና ለአዳዲስ ኢንቨስተሮች የሚደረጉ ማበረታቻዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የታየው መነቃቃት የሀገርን እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ መሰረት የሚያኖር መሆኑን ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሃላፊ እንዲሪስ አብዱ፤ በክልሉ የኢንቨስትመንት ዘርፉ አበረታች ውጤት እንዲያመጣ በተቀናጀና በተደራጀ መልኩ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ 10 ወራት ብቻ በክልሉ 288 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ጥያቄ አቅርበው እየተስተናገዱ መሆኑን አንስተዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ በድሉ ውብሸት፤ በበኩላቸው በከተማዋ በተለይም ለኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰጠው ትኩረትና እየተመዘገበ ያለው ውጤት ጥሩ የሚባል መሆኑን ተናግረዋል።
በተያዘው በጀት ዓመት እስካሁን 25 አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ስራ ጀምረው ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ገልጸዋል።
በአማራ ክልል በለፉት 10 ወራት 151 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸው ታውቋል።
ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...
Sep 11, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...
Sep 10, 2026
ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...
Sep 7, 2026
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...
Aug 31, 2026