የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

ስራ አጥነትን መቅረፍ የሚያስችሉ አሰራሮችን በመተግበር ውጤት እየተመዘገበ ነው - ሚኒስቴሩ

May 30, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፤ ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፦ የስራ ፈጠራ አማራጮችን ወደ ውጤት መቀየር የሚያስችሉ አሰራሮችን በመተግበር ስራ አጥነትን ለመቅረፍ እየሰራ መሆኑን የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ እና በኦሞ ባንክ የተዘጋጀ የወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ፣ ብድር ስርጭትና አመላለስ ላይ ያተኮረ ክልላዊ የንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡


በሚኒስቴሩ የስራ ስምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ በመርሃ ግብሩ ላይ የስራ ፈጠራ አማራጮችን ወደ ውጤት መቀየር የሚያስችሉ አሰራሮችን በመተግበር ስራ አጥነትን ለመቅረፍ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ለተግባራዊነቱም የክህሎት፣ የስልጠናና የገበያ ትስስር ድጋፍ መደረጉንና ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ የፈጠራ ውጤቶችን ለማጠናከርም የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ፖሊሲ መቀረጹን አስረድተዋል፡፡

በተለያየ የስራ መስክ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞችን ሽግግር ለማስፋት የብድር አቅርቦትና ስርጭት፣ የዕርስ በርስ ልምድ ልውውጥና ምርቶችን የማስተዋወቅ ስራዎች መኖራቸውን ገልጸዋል፡፡


የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና የመንግሥት ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር) በበኩላቸው በክልሉ የዜጎችን የስራ አጥነት ችግር በመቅረፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡

በተለይም ጸጋዎችን ወደ ልማት ለመቀየር ድጋፍና ክትትል እንዲሁም የመነሻ ካፒታል የማቅረብ ስራ መሰራቱንም ጠቁመዋል፡፡


የክልሉ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ ሙስጠፋ ሀሰን በክልሉ የስራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ በአካባቢው የሚገኙ ፀጋዎችን ለይቶ መጠቀም የሚያስችል ዕቅድ በማዘጋጀት ዘላቂና አስተማማኝ የስራ ዕድልን ለመፍጠር ትኩረት መደረጉን ተናግረዋል፡፡

በክልሉ የስራ ሀሳብን ወደ ሀብት መቀየር እንዲቻል በተደረገው ጥረት በርካታ ኢንተርፕራይዞች ከጥቃቅን ተቋምነት ተነስተው ወደ ኢንደስትሪ ደረጃ ማደግ መቻላቸውንም ተናግረዋል፡፡

የኦሞ ባንክ ፕሬዚዳንት አብርሃም አላሮ በበኩላቸው ባንኩ የተለያዩ የብድር አማራጮችን በማቅረብ የዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የበኩሉን ለመወጣት የሚያደርገውን ጥረት ያጠናክራል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026