የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በኢንቨስትመንት ዘርፍ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው ሪፎርም ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን እየፈጠረ ነው - ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር)

Jun 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 23/2017(ኢዜአ)፦መንግስት በኢንቨስትመንት ዘርፍ ተግባራዊ እያደረገ ያለው ሪፎርም ምቹ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ከባቢ እየፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ገለፁ።

የኦሮሚያ ክልል የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴና አማራጮች ዙሪያ ፎረም ተካሂዷል።


በፎረሙ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አሕመድ እድሪስ እና ባለሃብቶች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት እንደ ሀገር ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት በርካታ የሪፎርም ተግባራት መከናወኑን ተናግረዋል።

የህግን ጨምሮ የፖሊሲ፣ የአሰራር እና ሌሎች አስፈላጊ ማሻሻያዎች መደረጋቸውን አንስተዋል።

ማሻሻያዎቹ ተገማች የሆነ የኢንቨስትመንት እና የቢዝነስ ከባቢን ለመጥፈር እያስቻሉ መሆናቸውንም ገልጸው፤ ባለሃብቶች በምቹ ሁኔታ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችል መሆኑንም አስታውቀዋል።

ባለሃብቶች ይህን እድል በመጠቀም ኢንቨስት እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡


የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ በበኩላቸው ከለውጡ ወዲህ እንደ ሀገር የተወሰዱ የኢንቨስትመንት ማሻሻያዎች የኢንዱስትሪ ዘርፉን በከፍተኛ መጠን ማነቃቃቱን አንስተዋል።

በተለይ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪውን ምርታማ እንዲሆን፣ የዘርፉ ማነቆዎች እንዲፈቱ እና ለተጨማሪ ኢንቨስትመንቶች ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አስታውቀዋል፡

ይህንን ተከትሎ በኢንዱስትሪ ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑንም ተናግረዋል።

መንግስት ኢንዱስትሪዎች የሚያጋጥማቸውን ችግር ለመፍታት የአምራች ኢንዱስትሪ ምክርቤት በማቋቋም እየሰራ እንደሚገኝም ጨምረው ገልጸዋል።


የኦሮሚያ መሬት ቢሮ ኃላፊ መሰረት አሰፋ እንዳሉት ቢሮው ከኢንቨስትመንት ቢሮ ጋር በቅንጅት ኢንቨስተሮች በክልሉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ አስራር ተዘርግቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026