የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአሮሚያ ክልል 17 አነስተኛና መካከለኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች በዚህ ዓመት መጨረሻ ይጠናቀቃሉ

Jun 3, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ ግንቦት 24/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል እየተገነቡ ከሚገኙ 51 የአነስተኛና መለስተኛ የመስኖ ግድቦች መካከል 17ቱ በዓመቱ መጨረሻ ተጠናቀው ለአገልግሎት እንደሚበቁ የክልሉ የመስኖና አርብቶ አደሮች ቢሮ ገለጸ።

የቢሮው ኃላፊ ኢንጂነር ግርማ ረጋሳ በኢሉአባቦር ዞን ዳሪሙ ወረዳ እየተገነባ የሚገኘውን የሆማ ሆቢ ፊና ፕሮጀክት ግንባታ ያለበትን ደረጃ ተመልክተዋል።

የክልሉ መንግስት 'ፊና ፕሮጀክት' በተሰኘ መርሃ-ግብር በክልሉ ቆላማ እና የአርብቶ አደር አካባቢዎች አነስተኛና መለስተኛ የመስኖ ግድቦችን ገንብቶ የማህበረሰቡን የውኃ ችግር ለመቅረፍ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም በክልሉ የተለያዩ ዞኖች 51 አነስተኛ እና መለስተኛ የመስኖ ግድቦች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።


በግንባታ ላይ ከሚገኙ የመስኖ ፕሮጀክቶች መካከል 17ቱ በዓመቱ መጨረሻ ላይ ተጠናቀው ለአገልግሎት እንደሚበቁ ገልጸዋል።

የክልሉ መስኖና አርብቶ አደሮች ቢሮም ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ጠንካራ የክትትልና ድጋፍ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አመልክተዋል።

በኢሉአባቦር ዞን ዳሪሙ ወረዳ በ175 ሚሊዮን ብር እየተገነባ የሚገኘው የሆማ ሆቢ ፊና ፕሮጀክት ግንባታው ከተጀመረ ሁለት ዓመታትን ማስቆጠሩን ጠቅሰዋል።


ግንባታው ገና 37 በመቶ ላይ በመሆኑ በአስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲጠናቀቅ የሚያስችል ስራ እንደሚሰራም ተናግረዋል።

በኢሉአባቦር ዞን በአጠቃላይ ከ2 ሺህ 200 ሔክታር በላይ መሬት ማልማት የሚያስችሉ አነስተኛና መለስተኛ የመስኖ ግድቦች እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መሐመድጠሃ አባፊጣ ተናግረዋል።

ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እየተሰራ በሚገኘው ስራ ተጨማሪ ትልቅ አቅም የሚፈጥሩ ስለመሆናቸውም አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026