የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአሮሚያ ክልል 17 አነስተኛና መካከለኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች በዚህ ዓመት መጨረሻ ይጠናቀቃሉ

Jun 3, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ ግንቦት 24/2017(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል እየተገነቡ ከሚገኙ 51 የአነስተኛና መለስተኛ የመስኖ ግድቦች መካከል 17ቱ በዓመቱ መጨረሻ ተጠናቀው ለአገልግሎት እንደሚበቁ የክልሉ የመስኖና አርብቶ አደሮች ቢሮ ገለጸ።

የቢሮው ኃላፊ ኢንጂነር ግርማ ረጋሳ በኢሉአባቦር ዞን ዳሪሙ ወረዳ እየተገነባ የሚገኘውን የሆማ ሆቢ ፊና ፕሮጀክት ግንባታ ያለበትን ደረጃ ተመልክተዋል።

የክልሉ መንግስት 'ፊና ፕሮጀክት' በተሰኘ መርሃ-ግብር በክልሉ ቆላማ እና የአርብቶ አደር አካባቢዎች አነስተኛና መለስተኛ የመስኖ ግድቦችን ገንብቶ የማህበረሰቡን የውኃ ችግር ለመቅረፍ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም በክልሉ የተለያዩ ዞኖች 51 አነስተኛ እና መለስተኛ የመስኖ ግድቦች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።


በግንባታ ላይ ከሚገኙ የመስኖ ፕሮጀክቶች መካከል 17ቱ በዓመቱ መጨረሻ ላይ ተጠናቀው ለአገልግሎት እንደሚበቁ ገልጸዋል።

የክልሉ መስኖና አርብቶ አደሮች ቢሮም ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ጠንካራ የክትትልና ድጋፍ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አመልክተዋል።

በኢሉአባቦር ዞን ዳሪሙ ወረዳ በ175 ሚሊዮን ብር እየተገነባ የሚገኘው የሆማ ሆቢ ፊና ፕሮጀክት ግንባታው ከተጀመረ ሁለት ዓመታትን ማስቆጠሩን ጠቅሰዋል።


ግንባታው ገና 37 በመቶ ላይ በመሆኑ በአስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲጠናቀቅ የሚያስችል ስራ እንደሚሰራም ተናግረዋል።

በኢሉአባቦር ዞን በአጠቃላይ ከ2 ሺህ 200 ሔክታር በላይ መሬት ማልማት የሚያስችሉ አነስተኛና መለስተኛ የመስኖ ግድቦች እየተከናወኑ መሆኑን የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መሐመድጠሃ አባፊጣ ተናግረዋል።

ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እየተሰራ በሚገኘው ስራ ተጨማሪ ትልቅ አቅም የሚፈጥሩ ስለመሆናቸውም አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026