የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኢንቨስትመንት ዘርፍ የግል ባለሃብቶች እያደረጉት ያለው ተሳትፎ የሚበረታታ ነው

Jun 3, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ግንቦት 24/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኢንቨስትመንት ዘርፍ የግል ባለሃብቶች እያደረጉት ያለው ተሳትፎ የሚበረታታ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።


በአሶሳ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የፌዴራል፣የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈጻሚዎች የጋራ የምክክር መድረክ ዛሬ ተጠናቋል።


የመድረኩ ተሳታፊዎች ከውይይቱ በተጓዳኝ በክልሉ በባለሃብቶች እየለሙ የሚገኙ የኢንቨስትመንት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።


ከተጎበኙት የኢንቨስትመንት ስራዎች መካከል በሆሞሻ ወረዳ የሚገኘው ፍቃዱ ነመራ የተቀናጀ የእርሻ ልማት ድርጅት እና በአሶሳ ከተማ የሚገኘው የእምነበረድ ፋብሪካ ይገኙበታል።


የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ዝናቡ ይርጋ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለፁት፥ባለሃብቶች የክልሉን የተፈጥሮ ሀብት በመጠቀም በኢንቨስትመንት ዘርፍ መሠማራታቸው ለክልሉ የኢኮኖሚ አቅም መጠናከር ያግዛል።


ክልሉ በሁሉም አማራጮች ለኢንቨስትመንት ምቹ መሆኑን የተናገሩት ምክትል ኮሚሽነሩ፥በቀጣይም ዘርፉን በቴክኖሎጂ በማዘመን ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት ሊደረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።


በተለይም የክልሉን የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ የሚያደርጉ የኢንቨስትመንት ስራዎች በሁሉም አካባቢ ሊስፋፉ እንደሚገባ ጠቁመዋል።


ኮሚሽኑ በሁሉም የሀገሪቷ አካባቢዎች የሚገኙ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለሀገር ውስጥ እና ለውጪ ባለሃብቶች የማስተዋወቅ ስራ እያከናወነ መሆኑንም ጠቅሰዋል።


ከጉብኝቱ ተሳታፊዎች መካከል የሶማሌ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዘይነብ ሐጂአደን እና የጋምቤላ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ተወካይ ኡፒየው ኡነክ እንደተናገሩት፥ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለው የተፈጥሮ ሀብት ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት ያግዛል።


በተለይም ክልሉ ለግል ባለሃብቶች የፈጠረው ምቹ ሁኔታ እንደ ተሞክሮ የሚወሰድ መሆኑን ጠቁመው፥ የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በዘርፉ ቢሰማሩ ውጤታማ እንደሚሆኑ አይተናል ብለዋል።


ለሁለት ቀናት በነበራቸው የኢንቨስትመንት ኮሚሽን የምክክር መድረክም በዘርፉ ላይ የነበሩ ክፍተቶችን በማረም እና ምቹ ሁኔታ በመፍጠር የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲጨምር የሚያስችል ውይይት ማድረጋቸውን ተሳታፊዎቹ ተናግረዋል።


በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች፣ የፌዴራል፣የክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች የዘርፉ አመራሮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026