የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በባሕርዳር ከተማ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የሌሎችም ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ ቀጥሏል

Jun 4, 2025

IDOPRESS

ባሕርዳር፤ ግንቦት26/2017(ኢዜአ)፡- በባሕርዳር ከተማ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የሌሎችም ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ባለሃብቱንና ሌላውንም ማህበረሰብ በማስተባበር ተጠናክሮ መቀጠሉን የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ።

በከተማው እየተከናውኑ በሚገኙ ዋና ዋና ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ዙሪያ በየደረጃው የሚገኙ አመራር አባላት የተሳተፉበት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።


በመድረኩ ላይ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው እንዳሉት ፤ በባሕር ዳር ከተማ ሰፋፊና በውጤታማነት የቀጠሉ የተለያዩ የልማት ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛል።

እነዚህም በከተማው የነዋሪዎችን የልማት ፍላጎት እና የከተማዋን ዘላቂ እድገት መሰረት በማድረግ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎችንም ታላላቅ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች እንደሆኑ ጠቅሰዋል።

የልማት ስራዎቹ ነዋሪዎችንና ባለሃብቱን በማሳተፍ የበለጠ ተጠናክረው እንደቀጠሉ ገልጸው፤ ይህንን ይበልጥ በውጤታማነት ለማስቀጠል ገቢ የመሰብሰብ አቅም ማጎልበት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ተሻገር አዳሙ በበኩላቸው፤ በከተማው በመጀመሪያውና በሁለተኛው ምዕራፍ 22 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ለማከናወን ታቅዶ እየተተገበረ እንደሚገኝ ተናግረዋል።


ዕቅዱን ለማሳካት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ የአስፋልት መንገዶች ግንባታ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አንስተው፤ የልማት ስራዎቹ የከተማዋን እድገት የሚያፋጥኑ እንደሆኑ አስረድተዋል።

በተለይም ከተማዋን ከጣና ሀይቅ ጋር ቀጥታ በማገናኘት ለጎብኝዎችም ሆነ ለነዋሪዎች ይበልጥ ምቹ እያደረገ መሆኑን አብራርተዋል።

ለልማት ስራዎቹ ባለሀብቶች ፣ ነጋዴዎችና ሌሎችም ነዋሪዎች አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላለፈዋል።

በመድረኩ የክልል ፣ የከተማ አስተዳደሩና የክፍለ ከተሞች አመራር አባላት እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026