የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በምሥራቅ ጎጃም ዞን ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ በኩታ ገጠም አሰራር የተጠናከረ ተግባር እየተከናወነ ነው

Jun 9, 2025

IDOPRESS

ደብረማርቆስ፤ግንቦት 30/2017(ኢዜአ)፡-በምሥራቅ ጎጃም ዞን በ2017/2018 የምርት ዘመን ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ በኩታ ገጠም አሰራር የተጠናከረ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።


ምርትና ምርታማነት እያሳደገላቸው ያለውን የኩታ ገጠም አሰራርን አጠናክረው መቀጠላቸውን በዞኑ አርሶ አደሮች ተናግረዋል።


በምሥራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ እንቢያለ አለኸኝ እንደገለጹት፥በምርት ዘመኑ የኩታ ገጠም አሰራርን በማጠናከር ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል።


በዚህም በ2017/2018 የምርት ዘመን 435 ሺህ ሄክታር መሬትን በኩታ ገጠም ለማልማት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ተናግረዋል።


ይህም በምርት ዘመኑ አጠቃላይ በዘር ለመሸፈን ከታቀደው ከ640 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ውስጥ እንደሆነ ጠቁመዋል።


እስካሁን ባለው ሂደትም ከ40 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ ከ31ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ ቀድመው በሚዘራ የማሽላና የበቆሎ ሰብል በኩታ ገጠም መሸፈኑን አስታውቀዋል።


በኩታ ገጠም እየለማ ካለው የሰብል ዓይነት መካከል ጤፍ፣ ስንዴ፣ ማሽላ፣ በቆሎና የቢራ ገብስ እንደሚገኝበት ጠቅሰዋል።


በኩታ ገጠም ከሚሸፈነው መሬት ላይም ከ18 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ጠቁመው፥ለስኬቱም ሁሉን አቀፍ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።


በዞኑ የጎዛመን ወረዳ የገራሞ ቀበሌ አርሶ አደር ታከለ አቦዝን ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፈው ዓመት ከአንድ ሄክታር በላይ መሬታቸውን በኩታ ገጠም ስንዴን በመዝራት በጋራ በማረም፣ ተባይ በመቆጣጠርና ግብአት በመጠቀም ውጤታማ መሆናቸውን አስታውሰዋል።


ይህም ከዚህ በፊት ያገኙት ከነበረው እስከ ስድስት ኩንታል ጭማሪ እንዳለው ጠቅሰው፤ በዚህ ዓመት ተሞክሮውን በማስፋት በኩታ ገጠም አሰራር ግማሽ ሄክታር መሬታቸውን ላይ በቆሎ መዝራታቸውን ገልጸዋል።


የኩታ ገጠም አሰራርን ከጀመሩ ባለፉት ሶስት ዓመታት ወዲህ ከሚያለሙት ሰብል በፊት ያገኙት ከነበረው ከአራት ኩንታል በላይ ብልጫ ያለው ምርት በማግኘት ተጠቃሚ እንደሆኑ የተናገሩት በደጀን ወረዳ የኩራር ቀበሌ አርሶ አደር ወርቁ ደስታ ናቸው።


ዘንድሮ ደግሞ ከአንድ ሄክታር በላይ ማሳታቸውን በኩታ ገጠም ማሽላ መዝራታቸውን ጠቁመው፤ የባለሙያ ምክረ ሃሳቦችንና ቅንጅታዊ አሰራርን በመተግበር ጭምር ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ እየተጉ መሆኑን ገልጸዋል።


በምሥራቅ ጎጃም ዞን በምርት ዘመኑ በአጠቃላይ ለማልማት ከታቀደው መሬት ላይ ከ25 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026