የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

አርሶ እና አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የገጠር ፋይናንስ ማስተባበሪያ ተቋቁሟል - ግብርና ሚኒስቴር

Jun 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፦ በአነስተኛ ማሳ የሚያመርቱ አርሶ እና አርብቶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የገጠር ፋይናንስ ማስተባበሪያ መቋቋሙን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።


በአነስተኛ ማሳ የሚያመርቱ አርሶ እና አርብቶ አደሮች የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነትና የፋይናስ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።


የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) የግብርና እና ገጠር ልማት አጀንዳ ወቅታዊና አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።


በኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አርሶ አደሮች በአነስተኛ ማሳ ላይ እንደሚያመርቱ ገልጸው፣ ሀገሪቱ በጀመረቻቸው ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ለገጠር ልማትና ግብርና ዘርፍ ልዩ ትኩረት መስጠቷን አንስተዋል።


የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የግብርና ግብዓቶቸን በማሟላትና የብድር አቅርቦትን በማሳደግ በኩልም በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል ነው ያሉት።


የመሬት አጠቃቀም አዋጅ መጽደቅ እንዲሁም የግብርና እና ገጠር ልማት ፖሊሲ ተግባራዊ መደረግ በአነስተኛ ማሳ የሚያመርቱ አርሶ እና አርብቶ አደሮችን በፋይናንስ ዘርፉ ተጠቃሚ ማድረግ ያስቻለ መሆኑን አመልክተዋል።


ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በየዓመቱ የምትተክላቸው ችግኞች የአርሶ አደሮችን ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ ባለፈ በምግብ ራስን ለመቻል የምታደርገውን ጥረት እያገዘ ነው ብለዋል።


አነስተኛ ማሳ ያላቸውን አርሶ እና አርብቶ አደሮች የፋይናንስና የኢንሹራንስ ተጠቃሚ በማድረግ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ አደጋዎች የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ እየተሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።


ለዚህም የገጠር ፋይናንስ ማስተባበሪያ ዩኒት መቋቋሙን ነው ያነሱት።


የገጠር ፋይናንስ ማስተባበሪያው ለአርሶ አደሮች የብድር አቅርቦት ተደራሽነትን ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።


የግብርና አደጋ ስጋትን የሚቀንስ የኢንሹራንስ አገልግሎትን በማሳደግ አርሶ አደሩ በአየር ንብረት ለውጥ የሚደርስበትን ጉዳት መቀነስ እንደሚያስችልም አንስተዋል።


የማስተባበሪያ ማዕከሉም የአርሶ አደሮችን የመረጃ አያያዝ ሥርዓት እንደሚያጠናክር ገልጸው፥ ለዘላቂና ስኬታማ ስራ የባለድርሻ አካላት ትብብርና ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ ነው ብለዋል።


የጌትስ ፋውንዴሽን ከፍተኛ ፕሮግራም ኦፊሰር ሳሚ ሲምቤ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በግብርናው ዘርፍ አስድናቂ ለውጦችን እያሳየች መሆኑን አንስተዋል።


የተገኙ ስኬቶችን ለማጠናከር አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮችን የአደጋ ተጋላጭነት በተቀናጀ መልኩ መቀነስ ይገባል ብለዋል።


የአየር ንብረት ለውጥ በአነስተኛ ማሳ በሚያመርቱ አርሶ አደሮች ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስም የኢንሹራንስ አገልግሎትን ማስፋት፣ ተቋማትን ማጠናከርና ፖሊሲዎችን ማጎልበት ይገባል ነው ያሉት።


የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ(ዶ/ር) በበኩላቸው የግብርና ዘርፉ የስራ ዕድል በመፍጠርና የወጪ ንግዱን በማሳደግ ለኢኮኖሚ ዕድገቱ ዋነኛ ሞተር መሆኑን አንስተዋል።


ይህን ለማጠናከርም ለባለ አነስተኛ ማሳ አርሶ እና አርብቶ አደሮች የተቀናጀ የፋይናንስና የኢንሹራንስ አቅርቦትን ለማስፋት እየተሰራ ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያ መድህን ሰጪዎች ማህበር ፕሬዚዳንት ያሬድ ሞላ፥ የተቀናጀ የኢንሹራንስ አገልግሎትን መተግበር ለአርሶ አደሮች እፎይታ በመስጠት የግብርና ስራን ውጤታማ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026