የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ከእንስሳት ምርት የሚገኘው የውጭ ምንዛሪ እንዲጨምር አስችሏል - ኢኒስቲትዩቱ

Jun 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ከእንስሳት ምርት የሚገኘው የውጭ ምንዛሪ እንዲጨምር ማድረጉን የኢትዮጵያ እንስሳት ልማት ኢኒስቲትዩት ገለጸ።


በ2017 በጀት ዓመት 10 ወራት ከ100 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱንም ኢኒስቲትዩቱ አስታውቋል።


የኢኒስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አስራት ጤራ ለኢዜአ፤ በ2017 በጀት ዓመት ከሥጋ፣ ከዕርድ ተረፈ ምርት፣ ከማር፣ ከሰምና ሰም ውጤቶች፣ ከወተትና ወተት ተዋጽኦዎች 122 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅ ዶ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል።


በበጀት ዓመቱ 10 ወራት ውስጥ 100 ነጥብ 23 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸው ገቢው ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ28 በመቶ ብልጫ አለው ብለዋል።


እንደ ዶክተር አስራት ገለጻ 98 በመቶ የሚሆነው ገቢ የተገኘው ከበግ፣ ፍየል፣ ዳልጋ ከብቶችና የግመል ሥጋ ቀሪው ገቢ ከማር፣ ከግመል ወተትና ከዶሮ ምርቶች ነው።


ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ የተዘረጉ አሰራሮች ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር ተዳምሮ በመስኩ የሚገኘው የውጭ ምንዛሪ ግኝት እንዲጨምር ማስቻሉንም ጠቅሰዋል።


ለአብነትም ባለፈው በጀት ዓመት 10 ወራት የተገኘው ገቢ 63 ነጥብ 2 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደነበር አስታውሰው የ2017 በጀት ዓመት 10 ወራት ገቢ ወደ 100 ነጥብ 23 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ ማለቱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።


ለስኬቱ መገኘት መሰረቱ በሕገ ወጥ መንገድ ወደ ውጭ ይወጡ የነበሩ የእርድ እንስሳቶች ወደ ሕጋዊ ኤክስፖርት ቄራዎች መምጣት መጀመራቸውና በጥቁር ገበያውና በባንኮች መካከል ያለው የውጭ ምንዛሬ ተመን መቀራረብ መሆኑን ጠቅሰዋል።


ዶክተር አስራት እንደገለጹት የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ኳታር የኢትዮጵያን የእንስሳት ምርቶች በስፋት የሚገዙ ናቸው፡፡


ለቄራዎች የእርድ እንስሳትን በብዛት ለማቅረብ ነጋዴዎችና ህብረት ሥራ ማህበራትን የማስተሳሰር ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉንም አብራርተዋል።


የእርድ እንስሳት አቅርቦትን ለማሳደግ ኤክስፖርት ቄራዎችና አርብቶ አደሮች ውል ፈርመው በጋራ የሚሰሩበት የኮንትራት እርባታ አሰራር መዘርጋቱንም ተናግረዋል።


በሙከራ ደረጃም 120 የደቡብ ኦሞ አርብቶ አደሮች ወደ ኮንትራት እርባታ አሰራር እንዲገቡ መደረጉን ገልጸው ከደቡብ ኦሞ የሚገኘውን ተሞክሮ በመቀመር ወደ ሌሎች አካባቢዎች የማስፋት ሥራ እንደሚከናወንም አመልክተዋል።


የተሻሻለ ዝርያ እና ጤናው የተጠበቀ የእንስሳት እርባታ ሥርዓት በመዘርጋት ከዘርፉ የሚገኘው ጥቅም እንዲያድግ እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026