የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

አዲስ አበባ በፈጣን የመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ የምትገኝ አስደናቂ ከተማ ናት

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2017(ኢዜአ)፦አዲስ አበባ በፈጣን የመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ የምትጓዝ መንገዶቿ ሰላም የሰፈነባቸው አስደናቂ ከተማ ሆና አግኝተናታል ሲሉ የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ኃይማኖት አባቶች ገለጹ፡፡

በአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ምክር ቤት ስብሰባ በአዲስ አበባ ተካሄዷል።

በምክር ቤቱ ስብሰባ ከዓለም ዙሪያ ካሉ 55 የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን አባል ቤተ ክርስቲያናት ተወካዮች የተሳተፉበት ውጤታማ ኹነት እንደሆነም ተገልጿል፡፡

የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ጳጳስ ሄነሪክ ስቱብኬር ለኢዜአ እንዳሉት፤ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄደው የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ምክር ቤት ስብሰባ በኮቪድ ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጦ ቆይቷል።

የምክር ቤቱን ስብሰባ ዳግም ሲካሄድ ኢትዮጵያ ኹነቱን በጥሩ መንገድ ማስተናገድ እንደምትችል ታምኖባት መመረጧን ጠቁመዋል።

በዚህም የኢትዮጵያ መንግስትና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አስደናቂ ትብብር በመፍጠር የጉዞ ሰነዶች በቀላሉ ተጠናቀው ተሳታፊዎች ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ መቻሉን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ እጅግ አስደሳች ጊዜ ማሳለፋቸውን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ ተሳታፊዎች ደህንነታቸው ተጠብቆ ውብ አዲስ አበባ መመልከት መቻላቸውን ተናግረዋል።


የታንዛኒያ ኢቫንጀሊካል ሉተራን ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ እና የፌዴሬሽኑ የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ፕሬዚዳንት ፍሬድሪክ ሾ በአዲስ አበባ ከተማ ውበት እጅግ በጣም ተደንቄያለሁ ብለዋል፡፡

በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ተዘዋውሬያለሁ፤ በፈጣን የመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ መሆኗን በሚገባ ተመልክቻለሁ ነው ያሉት፡፡

በኢትዮጵያ የተሰሩ ስራዎች የለውጥ ምልክቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።


የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ዋና ጸሀፊ ቄስ ዶክተር አኔ በርክሀርድት በኢትዮጵያ ቆይታቸው አስደናቂ አገልግሎት አግኝተናል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ትልቁ አባል በመሆኑ በኢትዮጵያ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026