የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

አዲስ አበባ በፈጣን የመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ የምትገኝ አስደናቂ ከተማ ናት

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 11/2017(ኢዜአ)፦አዲስ አበባ በፈጣን የመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ የምትጓዝ መንገዶቿ ሰላም የሰፈነባቸው አስደናቂ ከተማ ሆና አግኝተናታል ሲሉ የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ኃይማኖት አባቶች ገለጹ፡፡

በአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ምክር ቤት ስብሰባ በአዲስ አበባ ተካሄዷል።

በምክር ቤቱ ስብሰባ ከዓለም ዙሪያ ካሉ 55 የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን አባል ቤተ ክርስቲያናት ተወካዮች የተሳተፉበት ውጤታማ ኹነት እንደሆነም ተገልጿል፡፡

የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ጳጳስ ሄነሪክ ስቱብኬር ለኢዜአ እንዳሉት፤ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄደው የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ምክር ቤት ስብሰባ በኮቪድ ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጦ ቆይቷል።

የምክር ቤቱን ስብሰባ ዳግም ሲካሄድ ኢትዮጵያ ኹነቱን በጥሩ መንገድ ማስተናገድ እንደምትችል ታምኖባት መመረጧን ጠቁመዋል።

በዚህም የኢትዮጵያ መንግስትና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አስደናቂ ትብብር በመፍጠር የጉዞ ሰነዶች በቀላሉ ተጠናቀው ተሳታፊዎች ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ መቻሉን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ እጅግ አስደሳች ጊዜ ማሳለፋቸውን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ ተሳታፊዎች ደህንነታቸው ተጠብቆ ውብ አዲስ አበባ መመልከት መቻላቸውን ተናግረዋል።


የታንዛኒያ ኢቫንጀሊካል ሉተራን ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ እና የፌዴሬሽኑ የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ፕሬዚዳንት ፍሬድሪክ ሾ በአዲስ አበባ ከተማ ውበት እጅግ በጣም ተደንቄያለሁ ብለዋል፡፡

በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ተዘዋውሬያለሁ፤ በፈጣን የመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ መሆኗን በሚገባ ተመልክቻለሁ ነው ያሉት፡፡

በኢትዮጵያ የተሰሩ ስራዎች የለውጥ ምልክቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።


የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ዋና ጸሀፊ ቄስ ዶክተር አኔ በርክሀርድት በኢትዮጵያ ቆይታቸው አስደናቂ አገልግሎት አግኝተናል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓለም አቀፍ ሉተራን ፌዴሬሽን ትልቁ አባል በመሆኑ በኢትዮጵያ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026