የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በኢትዮጵያ ለዘላቂ ልማት ስራዎች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ተመድ

Jun 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ለዘላቂና ሁሉን አቀፍ የልማት ስራዎች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) አስታወቀ።


ተመድ በኢትዮጵያ የተለያዩ ዘላቂ የልማት ስራዎችን መደገፍ የሚያስችል የስድስት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ዶላር የድጋፍ ስምምነት አድርጓል።


ስምምነቱን የተመድ ረዳት ዋና ጸሀፊ እንዲሁም በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ አስተባባሪ ዶክተር ራሚዝ አላካባሮቭ እና የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ፈርመውታል።


ስምምነቱ ኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለውና ሁሉን አቀፍ ልማት ለማረጋገጥ የምታደርገውን ጥረት የመደገፍ ዓላማ እንዳለው ተገልጿል።


ለአምስት አመት በሚተገበረው ስምምነት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚን ለማሳደግ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ለኢነርጂ ልማት፣ ለትምህርት፣ ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል እና ለሌሎች ዘርፎች እንደሚውልም ተመላክቷል።


የተመድ ረዳት ዋና ጸሀፊ እንዲሁም በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ አስተባባሪ ዶክተር ራሚዝ አላካባሮቭ በወቅቱ እንደገለጹት ድጋፉ የኢትዮጵያ የልማት ስራዎችን ለማገዝ ያስችላል።


በቀጣይም ተመድ በኢትዮጵያ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።


የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በበኩላቸው፤ የትብብር ስምምነቱ ኢትዮጵያ ለምታከናውናቸው የልማት ስራዎች ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።


የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው፤ ለስምምነቱ ውጤታማነት በትኩረት ይሰራል ብለዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026