የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የመዲናዋን ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ማዕከልነት የሚመጥኑ ናቸው

Jun 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የመዲናዋን ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ማዕከልነት የሚመጥኑ መሆናቸውን ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላት ገለጹ።

ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጋር የተወያዩ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላት የሃላላ ኬላ ኢኮ-ቱሪዝም ሪዞርት እና የጊቤ-3 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎብኝተዋል።

በዚሁ ጊዜ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላት በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተገነቡ የልማት ስራዎች ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን አንስተዋል።

በተለይም በአዲስ አበባ የተገነቡ እና በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ከተማዋ ተጭኗት የነበረውን ጎስቋላ ገጽታ በመቀየር ዓለም አቀፍ ስምና ዝና እንድትጎናጸፍ የሚያስችላት ናቸው ብለዋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአጭር ጊዜ በጥራትና በፍጥነት የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የመዲናዋን ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ማዕከልነት የሚመጥኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የአፋር ነፃ አውጪ ግንባር ፓርቲ ምክትል ሰብሳቢ ሀጂ እስማዔል መሀመድ አዲስ አበባ ከተማ በጭር ጊዜ ውስጥ ያስመዘገበችው የልማት ስኬት እንዳስደመማቸው ተናግረዋል።

በቀጣይም ኢትዮጵያ ለምታከናውናቸው የልማት ስራዎች የበኩላቸውን ገንቢ ሚና በመወጣት ለዜጎች የጋራ ተጠቃሚነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

በፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የወጣቶች ክንፍ ምክትል ሰብሳቢና የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ የወጣቶች ክንፍ ኃላፊና የሥራ አስፈፃሚ አባል ጥጋቡ ደጀኔ በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል።

በተጨማሪም የአዲስ አበባን ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ማዕከልነት በማሳደግ ለሌሎች ከተሞች ዕድገት ምሳሌ እንደሚሆን ገልጸዋል።

በጋምቤላ ክልል የኢዜማ ምክትል መሪ ጋትቤል ቦል በበኩላቸው አዲስ አበባን ውብ ገጽታ አንድትላበስ ላስቻሉ መሪዎችና የልማት አጋሮች ሁሉ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026