የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ግልገል ጊቤ ሦስት በዚህ ዓመት 7 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ችሏል

Jun 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 16/2017 (ኢዜአ)፦የግልገል ጊቤ ሦስት ኃይል ማመንጫ ግድብ በዚህ ዓመት 7 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ለኢኮኖሚው እንቅስቃሴ መሳለጥ ጉልህ ሚና መወጣቱን የኃይል ማመንጫ ግድቡ ሥራ አስኪያጅ ሃብታሙ ሰሙ ገለጹ።

ኬንያን ጨምሮ ለቀጣናው ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብም ትልቅ ሚና እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል።

የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቡ የታዳሽ ኃይልን በማሳደግና የበካይ ጋዝ ልቀትን በመቀነስ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።

የግልገል ጊቤ ሦስት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ሀብታሙ ሰሙ፥ ግድቡ በ2009 ዓ.ም ተጠናቅቆ አገልግሎት መጀመሩን አውስተዋል።


በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ላይ ከፍተኛውን ድርሻ በመያዝ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ አዎንታዊ ሚና እየተወጣ የሚገኝ ግዙፉ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።

ግድቡ 1 ሺህ 870 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ቀጥሎ ግዙፉ የኃይል ማመንጫ መሆኑን ተናግረዋል።

የግልገል ጊቤ ሦስት ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት 50 በመቶ በመሸፈን ለጎረቤት ሀገራትም ኃይል በማቅረብ ከፍተኛ ሚና እየተወጣ ነው ብለዋል።

የኃይል ማመንጫ ግድቡ የሥራ ሂደትም በኢትዮጵያውያን ብቁ ባለሙያዎች እየተመራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።


ግልገል ጊቤ ሦስት እያደገ ለሚገኘው ሀገራዊ የኤሌክትሪክ ፍላጎት ምላሽ በመስጠት ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑንም ጠቅሰዋል።


በዚህ ዓመትም 7 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማመንጨት ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴው ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.