የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከአሜሪካው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ትብብር ጋር በጋራ ለመሥራት ተፈራረመ

Jun 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከአሜሪካው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ትብብር ኩባንያ ጋር በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ በጋራ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ።

ሥምምነት መርሃ ግብሩ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በተገኙበት በአንጎላ ሉዋንዳ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ ጎን ለጎን ነው የተከናወነው።

ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) እና የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ትብብር ኩባንያ ጋሬት ጊሽ ፈርመውታል።

ሥምምነቱን ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ትብብር ተቋም ጋር ከ200 ሚሊየን ዶላር በላይ በሆነ ካፒታል በኢትዮጵያ በሆቴልና ቱሪዝም ኢንዱስትሪ ለመሰማራት የሚያስችለው መሆኑ ተገልጿል።


የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ሥምምነቱ ኢትዮጵያ የምትፈልገውና ከልማት ፕሮግራሟ ጋር አብሮ የሚሄድ ትልቅ የኢንቨስትመንት ሥምምነት መሆኑን አንስተዋል።

ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ እያስመዘገበች ያለውን አዎንታዊ ውጤት ይበልጥ ወደፊት አጠናክሮ ለማስቀጠል ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ አበረታች ውጤት እያስመዘገበች ባለበት ወቅት መፈረሙን ጠቅሰዋል።

በመሆኑም ዛሬ የተደረሰው ሥምምነት በዘርፉ የተመዘገቡ አበረታች ውጤቶች ለማስቀጠል እንደሚያስችል ጠቅሰው፤ ኩባንያው በኢትዮጵያ የሚያደርገው ተሳትፎ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካም ጭምር ተጽዕኖ ሊኖረው እንደሚችል ተናግረዋል።


የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ትብብር ፕሬዝዳንትና ሥራ አስፈጻሚ ጋሬት ጊሽ በበኩላቸው ሥምምነቱ አሜሪካ አፍሪካን በተመለከተ ለማጠናከር ያሰበችውን የንግድና ኢንቨስትመንት ዲፕሎማሲ የተከተለ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህንንም ተከትሎ ኩባንያው በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ተሳትፎው ለአፍሪካና ለኢትዮጵያ የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ እድገት የበኩሉን አስተዋጽዖ እንደሚያደርግ ያላቸውን እምነት መግለጻቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.