የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከአሜሪካው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ትብብር ጋር በጋራ ለመሥራት ተፈራረመ

Jun 25, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 17/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከአሜሪካው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ትብብር ኩባንያ ጋር በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ በጋራ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ።

ሥምምነት መርሃ ግብሩ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በተገኙበት በአንጎላ ሉዋንዳ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ ጎን ለጎን ነው የተከናወነው።

ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) እና የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ትብብር ኩባንያ ጋሬት ጊሽ ፈርመውታል።

ሥምምነቱን ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ትብብር ተቋም ጋር ከ200 ሚሊየን ዶላር በላይ በሆነ ካፒታል በኢትዮጵያ በሆቴልና ቱሪዝም ኢንዱስትሪ ለመሰማራት የሚያስችለው መሆኑ ተገልጿል።


የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ሥምምነቱ ኢትዮጵያ የምትፈልገውና ከልማት ፕሮግራሟ ጋር አብሮ የሚሄድ ትልቅ የኢንቨስትመንት ሥምምነት መሆኑን አንስተዋል።

ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ እያስመዘገበች ያለውን አዎንታዊ ውጤት ይበልጥ ወደፊት አጠናክሮ ለማስቀጠል ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ አበረታች ውጤት እያስመዘገበች ባለበት ወቅት መፈረሙን ጠቅሰዋል።

በመሆኑም ዛሬ የተደረሰው ሥምምነት በዘርፉ የተመዘገቡ አበረታች ውጤቶች ለማስቀጠል እንደሚያስችል ጠቅሰው፤ ኩባንያው በኢትዮጵያ የሚያደርገው ተሳትፎ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካም ጭምር ተጽዕኖ ሊኖረው እንደሚችል ተናግረዋል።


የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ትብብር ፕሬዝዳንትና ሥራ አስፈጻሚ ጋሬት ጊሽ በበኩላቸው ሥምምነቱ አሜሪካ አፍሪካን በተመለከተ ለማጠናከር ያሰበችውን የንግድና ኢንቨስትመንት ዲፕሎማሲ የተከተለ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህንንም ተከትሎ ኩባንያው በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ተሳትፎው ለአፍሪካና ለኢትዮጵያ የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ እድገት የበኩሉን አስተዋጽዖ እንደሚያደርግ ያላቸውን እምነት መግለጻቸውን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026